Friday, October 26, 2012

ሐይማኖት ወይስ ኳስ…አንድ ሚያደርገን….



እኔን የሀይማኖት ጉዳይ በጣም እያሳሰበኝ ነው። አመለካከቴንም እየለወጠው ነው  ። ምንም እንኳን አያስፈልጉም ማለት ባልችልም ነገር ግን ሀይማኖት ሰዎችን የሚለያዩና የሚከፋፍል ከሆነ ምን ይሰራሉ ፤አሁን እንደምናየዉ ሰውን አንድ እያደረገ ያለው ኳስ እየሆነ መቷል ስለዚህ ሀይማኖትን ከማስፋፋት ይልቅ ትልልቅ የዕግር ኳስ ሜዳዎችን መገንባት ነው ሚሻለን፤  በቅርቡ እንደተመለከትነው ቢሄራዊ ቡድናችን  ዋልያዎቹ ሲያሸንፉ ያየነው ደስታ በእውነቱ እንዴት እንደገረመኝ አትጠይቁኝ  ማለቴ ያየሁት የኢትዬፒያዊነት ስሜት በእውነቱ አይቸው አላውቅም በጣም ነበር ደስ ያለኝ ።


ታዲያ ሃይማኖት ነው ኳስ ለኛ ሰዎች የሚያፈልገን፤በአሁኑ ሰአት አገራችን ላይ እንኳን በጣም ብዙ ሀይማኖቶች አሉ    የሀይማኖቶች መብዛት ግን ምንም አልጠቀመንም የበለጠ እያጠበበን መጣ እንጂ ………

ሀይማኖቶች ከተቋቋሙበት አላማ ወይም እውነት ወተው የገንዘብ መሰብሰቢያ  የዝሙትና የመዳሪይ ቦታዎች ሆነዋል ፤የፖለቲካ ማራመጃ  ሰውን አንድ ከማድረግ ይልቅ ዘረኝነትን ማስፋፊያ ከመሆን አልፈው ርካሽ ቦትዎች ሆነዋል እውነት አምላክ የትኛው ነው
እስኪ እናንት ሃይማኖተኞች እውነት ማን ነው ፈጣሪ ዘረኛ ፖለቲከኛ ነበር እንዴ ….እንደዚህ እርስ በእርሳችን እየተባላን  ሀይማኖት መሪ ነኝ አያሉ በስከጀርባ ተንኮልን ዘረኝነትን  ዝሙትን የምናስፋፋ ከሆነ ብንሞት ይሻለናል ። አሁን ሀይማኖት አለን ከምንለው ሰዎች
ያ ከሃዲ የተባለው ኦሾ አይሻልም እንዴ   እሱ ቢያንስ ሰዎችን በቆዳ ቀለማቸው አለየም ሰዎችን አንድ አድርጎ ነበር እኮ ። እስኪ የትኛው ሀይማኖት ነው እኛን አንድ እያደረገን ያለው….በፍጹም …..ስለዚህ አንድ ሆነን እንድንቀጥል የሚያደርገን ሀይማኖት ነው  ኳስ….
አሁንስ ደሞ ለማኝን ሀይማኖት እየለየን መርዳት  በመጀመራችን    ለማኞችም አለባበሳቸውን መለዋወጥ ጀምረዋል አሉ  ምክንያቱም ሀይማኖታችን እንደዚህ  እየለያየንና እየበታተነን ነውና….


ሀይማኖተኞች እንዳትቀየሙኝ    እውነቱን ነው  የምነግራችሁ……….