Wednesday, April 30, 2014

በቅሎን አባትህ ማን ነው? ቢሉት “አጎቴ ፈረስ ነው አለ” አሉ፤ ምንነትና ማንነት፡ የዘመኑ አንገብጋቢ ጥያቄ


Pro Mesfinከፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም
ሚያዝያ 2006
ምጽዓት የቀረበ ይመስላል፤ ብዙ ሰዎች ሳይጠየቁ በቁሎው የተጠየቀውን ጥያቄ ራሳቸውን ጠይቀው አጎቴ ፈረስ ነው የሚለውን መልስ እየመለሱ ናቸው፤ ስለምንነታቸውና ስለማንነታቸው በውስጣቸው አንድ አስጨናቂ ነገር እንዳለባቸው ግልጽ ነው፤ የጎዶሎነት ስሜት ስለሚሰማቸው የድረሱልኝ ጥሪ በጩኸት እያሰሙ ነው፤ ግንባር ቀዳሚ መለከት ነፊም አለ፤ እውነት ግን አይደፈጠጥም፤ እየዘለለ ያፈጥባቸዋል፤ አጎቴ ፈረስ ነው ባሉ ቁጥር፣ አባትህስ እያለ ያፈጥባቸዋል! በፈረስ አጎትነት የአህያን አባትነት መደምሰስ አይቻልም፤ ነገር አፍጥጦ ከመጣ አፍጥጦ ከመግጠም የተሻለ መልስ አይገኝለትም፤ ተቅለስልሰው ሊያልፉት ሲሞክሩ በኅሊና ውስጥ ተቀርቅሮ ይደበቃል፤ ለራስም ለማኅበረሰብም ክፉና ዘላቂ በሽታ ይሆናል፤ ኢትዮጵያዊነት ማንነቱን የሚክድ ኢትዮጵያዊ ሲያቃዠው ያድራል እንጂ ፍቆ አያጠፋውም፤ አንድ ጊዜ በጀኒቫ በአንድ የአበሻ ምግብ ቤት ስበላ አንድ ዱሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዬ የነበረ የኤርትራ ተወላጅ ሲገባ ተያየን፤ እየሳቅሁ ደሞ እዚህ ምን ልታደርግ መጣህ ስለው፣ ከዚህ ማምለጥ እኮ አይቻልም፤ አለኝ፤ እንዴት ብሎ!
ምንነት ከማንነት የተለየ ነው፤ ምንነት ከማንነት ይቀድማል፤ ምንድን ነህ? የሚለው ጥያቄ ከተመለሰ በኋላ ነው ማን ነህ? መልስ የሚያስፈልገው፤ የምንነትን ጥያቄ የማያውቁ የማንነትን ጥያቄ ፍልስፍና አዋቂዎች መስለው የተውሶ ሀረጎችን ጣል ጣል እያደረጉ ተደናግረው ለማደናገር ይሞክራሉ፤ ከንቱ ድካም ነው፤ ማንነት ከምን ተነሥቶ ነው ራሱን ችሎ የሚቆመው? ራስን ሳያውቁ ሌላውን ለማወቅ መሞከር፣ ራስን ሳያሳምኑ ሌላውን ለማሳመን መሞከር፣ ያልሆኑትን ለመሆን ከመሞከር የሚቀልለው ራስን መሆን ነው፡፡
በቁሎው አባትህ ማን ነው ተብሎ ሲጠየቅ የነፍሱ ቁስል ተነክቶበታል (ለነገሩ በቁሎ ነፍስ የለውም)፤ ለዚህ ነው እያወቀ ጥያቄውን የሳተው! አሁን ሌላ ጥያቄ ሊያስፈልግ ነው፤ በቁሎው የካደው አባቱን ብቻ ነው? በአባቱ በኩል አጎቱ አህያ ነው፤ በእናቱ በኩል አጎቱ ፈረስ ነው፤በቅሎ አንግዲሀ አጎቴ ፈረስ ነው ሲል የካደው አባቱን ብቻ አይደለም።
በቁሎ አጎቴ ፈረስ ነው አለ የተባለውን ሳስብ የአባቴ ሸክሊት የምትባለዋ በቁሎ ትዝ አለችኝ፤ ማይጨው ዘምታለች! እሷ ትዝ ስትለኝ የማላውቃቸውን ወላጆችዋንም አሰብሁ፤ አንድ ወንድ አህያና አንዲት ባዝራ (ሴት ፈረስ)፤ ለመሆኑ አጎቴ ፈረስ ነው ያለው አህያ አገሩ የት ይሆን? ለመሆኑስ አጎቴ ፈረስ ነው ሲል ምን ማለቱ ነው? የሸክሊትን ዘር በአጭሩ ብናየው እንደሚከተለው ይሆናል፤–
አንደኛበቁሎው በአባቱ በኩል አንድ ወንድና አንዲት ሴት አያት አህዮች አሉት፤
ሁለተኛበቁሎውበእናቱበኩልአንድወንድናአንዲትሴትፈረስአያቶችአሉት
ሦስተኛ አባቱ፣ አህያው፣
አራተኛ እናቱ ፈረስዋ (ባዝራዋ)፣
አምስተኛ አህያ አጎትና አህያ አክስት፣
ስድስተኛ ፈረስ አጎትና ፈረስ አክስት፣
ከአንድ በቁሎ ተነሥተን ወደአንድ አህያና ወደአንድ ፈረስ ተሸጋግረን ስንት አህያና ስንት ፈረስ አዛመድን!
ስለኢትዮጵያ ሕዝብ ጎንደሬው የሲዳሞ ሰው፣ መሀንዲሱ፣ የሕግ ባለሙያው ደመቀ መታፈሪያ ያደገበትንና ያየውን በልብ-ወለድም በታሪክም እያቀነባበረ ከአርባ ዓመታት በፊት ጀምሮ ደጋግሞ ጽፎበታል፤ ብዙዎቻችን አልተማርንበትም፤ አላሰብንበትም፤ አልተወያየንበትም።
በማእከላዊ እስር ቤት፣ ከዚያም በቃሊቲ ከአንድ የወላይታ ወጣት ጋር (በአለበት ይቅናውና) ወዳጅነት ጀምረን ነበር፤ ስለወላይታ ለመማር ፈልጌ ገና ጥያቄዎችን መጠየቅ ስጀምር ወላይታ ውስጥ ብዙ ጎሣዎች መኖራቸውን ነገረኝ፤ ብዙ ነገር ለመማር ተዘጋጅቼ ሳለሁ መቼም ሁሌም በባርነት ውስጥ ስላለን እንደፈቀድን ለመሆንና እንደፈቀድን ለማድረግ አይፈቀድልንምና ለያዩን (ይለያያቸውና)፤ ያሰብሁትን ሳልፈጽም ቀረሁ፤ ቢሆንም ወላይታ ብዙ ከሌሎች የኢትዮጵያ ጎሣዎች ጋር ዝምድና ያላቸው ጎሣዎች መኖራቸውን ለመገንዘብ ችያለሁ፤ የደመቀ መታፈሪያን ሀሳብ በትንሽዋ ወላይታ ውስጥ ለማየትና ሀሳቡን ለማረጋገጥ አስችሎኛል፤ መማር ለፈለገ ቃሊቲም ትምህርት ቤት ነው።
ከብዙ ዓመታት በፊት አንድ የተምቤን ሰው ከጻፈው እንደተገነዘብሁት፣ በአንድ ዘመቻ ጊዜ ከሸዋ ከዘመተ ሰው መወለዱን በዳዊት መጽሐፍ ላይ ተጽፎለት ያገኝና የቅኔ ትምህርቱን ሲጨርስ አባቱን ፍለጋ ወደሸዋ ይመጣል፤ ቡልጋ ይደርሳል፤ እየጠየቀ የአባቱን ዘመዶች ያገኛል፤ የአባቱ ልጅ (ወንድሙ) አዲስ አበባ መሆኑ ይነገረውና አዲስ አበባ ይመጣል፤ በእንግሊዝ አገር ተምሮ የተመለሰውን ወንድሙን ያገኛል፤ ሥራ ያስገባዋል፤ የፈረንጁን ትምህርት ይማራል፤ ራሱን ችሎ ይኖራል፤ ወንድሙን ከነልጁ ደርግ ይገድለዋል፤ የተምቤኑ ተወላጅ ለሸዋው ወንድሙ ለቅሶ ይቀመጣል።
ከአንድ ሳምንት በፊት አንዲት ሴት አራት ልጆች ይዛ በአጠገቤ ስታልፍ ሳቅ ብላ አንገትዋን ሰበር አድርጋ ሰላምታ አሳየችኝ፤ አወቅኋት፤ ከአምስት ስድስት ዓመታት በፊት በዚያው በእኔ ሰፈር አካባቢ ትለምን የነበረች የመቀሌ ሴት ናት፤ በዚያን ጊዜ አርግዛ ሳያት የመጣሽው ከነባልሽ ነው ወይ ብዬ ስጠይቃት ወንድ ልጅዋ አባቱ እንዳልመጣ ነገረኝ፤ እርግዝናዋ ድንገተኛ አደጋ መሆኑን ነገረችኝ፤ በጣም ትልቅ ሆና ስለነበረ ወደሀኪም ቤት እንድትሄድ ገንዘብ ሰጠኋት፤ ከወለደች በኋላም አንድ ጓደኛዬ መሣፈሪያ ሰጣትና ወደመቀሌ ተመለሰች፤ አሁን እንደገና መጣች፤ ስጠይቃት ሁሉም ነገር ተባብሷል፤ የማዳበሪያ እያሉ ያስጨንቁናል፤ አለች፤ በይ አሁን ደግሞ ተጠንቀቂ ብዬ ተሳስቀን ተለያየን፤ ችግርም ያዛምዳል።
እንደመደምደሚያ አድርጌ ቢትወደድ አስፍሐን ላንሣ፤ ቢትወደድ አስፍሐ ለኢጣልያ ያደሩ ባንዳ ነበሩ፤ በመጨረሻም በጎንደር ላይ ኢጣልያ ድል ሲሆን ከጌታቸው ጋር ነበሩ፤ ኢጣልያኑ ጌታቸው ወደአገሩ ሲሸሽ ቢትወደድ አስፍሐን ይዞ ለመሄድ ፈልጎ ነበር፤ ቢትወደድ አስፍሐ ግን ለሁለተኛ ጊዜ አልከዳም ብለው በአገራቸው ቀሩ፤ የዱሮዎቹ ሰዎች ያላቸው ሰብአዊነትና አብሮ የመኖር ጥበብ ቢትወደድ አስፍሐን ከራስ አበበ አረጋይ ጋር አገናኛቸው፤ ታላቁ ባንዳ የትግራይ ገዢ ለነበሩት ለታላቁ አርበኛ ረዳት ሆኑ፤ ራስ አበበ ስለቢትወደድ አስፍሐ ያላቸውን አስተያየት ለማወቅ ዕድሉ አልገጠመኝም፤ ቢትወደድ አስፍሐ ስለራስ አበበ ያላቸውን አስተያየት ግን በመጠኑም ቢሆን ለማወቅ ችዬአለሁ፤ ቢትወደድ አስፍሐ ራስ አበበን በጣም ያከብሩአቸዋል፤ በጣም ያደንቁአቸዋል፤ የቢትወደድ አስፍሐ አማርኛና የኢትዮጵያ ታሪክ እውቀት ሳይተላለፍልን በመቅረቱ በጣም አዝናለሁ፤ ስለኤርትራ ‹ናጽነት› ድምጽ እንዲሰጥ ወያኔ በሚገፋፋበት ጊዜ ቢትወደድ አስፍሐ በሙሉ መንፈሳዊ ወኔ የወያኔንና የሻቢያን ጫና ተቋቁመው ኢትዮጵያዊነታቸውን አልክድም ብለው በኩራት ቆሙ፤ ባንዳው አርበኛ ሆኑ! ንስሐ ያጸዳል! ንስሐ ነጻነትን ያጎናጽፋል፤ የደበቁት ኃጢአት ግን በቀን ያቃዣል!
ባንዳና የባንዳ ልጅ ሁሉ የአርበኛ ስም ሲጠራ ያቃዠዋል! አጎቴ ፈረስ ነው! ይላል።
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

Tuesday, April 29, 2014

የጌታን እናት ማርያምን ነገር ማን ያውቀዋል?!




ኤሎሄ! ቅዱስ! ኤልሻዳይ! አዶናይ! ያህዌ! ጸባዖት! ኢየሱስ! ክርስቶስ! አማኑኤል! በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ሥም! አሜን!
አቤቱ አባት ሆይ በሥጋ ትዛመደን ዘንደ ከእኛ ወገን በመረጥካት ቅድስት እናትህ ማርያም ሥም እንዲሁ እንደተዛመድከን መከራችንን ሁሉ ትቀበል ዘንድ በወደድክበት ፍቅርህ ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እለምንሀለሁ! አሜን!
በቅርቡ አንድ "ነገረ ማርያም የተባለው መተጽሐፍ ልዩ ወንጌል (ከወንጌል ያፈነገጠ) ነው" በማለት ስለ ነገረ ማሪያም የሚተች ጽኁፍ ከአንድ አባ ሰላማ ከሚል ደረ-ገጽ (www.abaselama.org/2014/03/blog-post_27.html‎) ማንበቤን ተከትሎ ይህንን አስተያየተን ለመሰንዘር ወደድኩ፡፡  በዚህ ዘመን ሀይማኖታዊ የሚመስሉ ነገሮችን በጥንቄ ማስተዋል እንዳለብን ስለአሳሰበኝ ይህችን ላካፍላችሁ በሚል፡፡ አነበብኩት ያለኳችሁን ነገረ ማርያምን የሚተቸው ጽሁፍ ብዙዎቻችሁ አንብባችሁታል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ትችቱን በደፈናው ለቃወም አይደለም፡፡ ሊያስተላልፍ የፈለገው መልዕክት የቅንነት ሳይሆን አንድ ነገርን መዞ ብዙ ሕዝብን ለማደናገር የታሰበ ስለመሰለኝ እንጂ፡፡ እርግጥ ይህ ጽሑፍ መነሻ ሆነኝ እንጂ ብዙ ሌሎች ተቃርኖአዊ የሆኑ መልዕክቶችን ስለሀይማኖት የሚያስተላልፉ በተለይም ደግሞ የጌታ እናት ነገር ከነዚያ አይሁዳውያን ቀናተኞች ባልተናነሰ የሚያናድዳቸው ብዙዎች ናቸው፡፡ ግን ምን ማድረግ ይቻላል ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር እናት ነች! ይሄንን ማን ሊሽረው ይችላል! ነገረ ማርያምም በሉት ሌላ ታሪክ ከዚህ እውነታ በላይ ስለጌታ እናት ማንነት ሊመሰክርልን የሚችል አይመስለኝም፡፡ ምንአልባት የአምላክ እናት የሆነችበትን ሆኔታዎች በሰውኛው ሊተነትኑልን ይሞክሩ ይሆናል እንጂ፡፡ የአምላክ እናት ለመሆን የበቃችበት ማንነቷ ግን ፈጣሪዋም ልጇም በነው እግዚአብሔር የሚታሰብ እንጂ በእኛ አእምሮ ሊታሰብ የሚችል እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡ ይህ ሚስጢር ነብያትንም በጨረፍታ እየመጣ ሲያስጨንቃቸው የኖረ ጉዳይ ነው፡፡ እሷ ራሷ እንኳን መልአኩ ነገራት እንጂ በፈጣሪዋ ዘንድ የዚህን ያህል የተከበረች እንደሆነች የተረዳችው አይመስልም፡፡ መልዐኩም ቢሆን ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም በማለት የተነገረውን ከሴቶች ሁሉ አንቺ የተባረክሽ ነሽ ብሎ ምስራቹን ነገራት እንጂ ሂደቱን ምን እንደነበር አልገጸውም፡፡ ኤልሳቤጥ የጌታን እናት ማንነት ለማየት የቻለቸው በመንፈስቅዱስ ኃይል ነበር፡፡ ኤልሳቤጥም የቱንም  ያህል የጌታ እናት ዘመዷና በእድሜም ልጇ ልትሆን ብትችልም ልተጎበኛት ወደቤቷ በመምጣቷ እጅግ የተደሰተችም ቢሆን ከራሷ ክብር ጋር አነጻጽራ የጌታዬ እናት ሆይ ወደእኔ ትመጭ ዘንድ እኔ ምንድነኝ ስትል ነበር የደነገጠችው፡፡ ኤልሳቤጥ ግን ከነበይም በላይ የሆነው የዮሐንስ እናት ነች፡፡  ዮሐንስ ስለጌታ ሲናገር የእግሩን ጫማ እንኳን ልፈታ የማይገባኝ እንዳለው ነበር እናቱ ኤልሳቤጥ የጌታን እናት በአየች ጌዜ የተናገረችው፡፡ ይህ እውነታ በሥጋ የሚታይ አይለም፡፡
ወደተነሳሁበት ጉዳይ ልመልሳችሁና ይህ አነበብኩት ያልኳችሁ ነገረማርያምን የሚተቸው ጽሑፍ መሠረታዊ ነገሩ ለመቃወም ብቻ ይመስላል፡፡ እንደዘመኑም ሀይማኖታዊ ነገር ላይ ትችት ለመሰንዘር ምንም የማይከብዳቸው አይነት ሰው የጻፈው የሚስላል፡፡ ሲጀምር ነገረ ማርያም የሚባለውን መጽሐፍ ተችው አንብበውት የሚያውቁ አይመስልም፡፡ ከአነበቡት ደግሞ ሆን ብለው ደብቀውታል፡፡ እንደእውነቱ አኔም ይህ ነገረ ማርያም የሚባለውን መጽሐፍ አንብቤው አላውቅም፡፡ እኔ በብዙ ፀሎት መፅሐፍት ላይ የተካተተው ነገረ ማርያም የሚለው የነገረ ማርያም ዋናው መጽሐፍ መሆኑንም አላውቅም፡፡ ይልቁንም ይህ በጸሎት መጽሐፍ የተካተተው ነገረ ማርያም እንዳለ በነገረ ማርያም በማለት ብዙ ዋቢዎችን ከነገረ-ማርያም፣ ከሌሎችም መጻሕፈት እያጣቀሰ የሚናገር እንደሆነ አንብቤያለሁ፡፡ ይህን በጸሎት መጽሐፍ የተካተተውን ነገረ-ማርያም ልብ ብላችሁ እንደሆነ የእመቤታችንን ታሪክ እስከ ወደ ቤተመቅደስ የገባችበትን ጊዜ ሊተርክ ይሞክርና ከዚያ ፍጹም ከዚህ ታሪክ ጋር የተቋረጠ ሌላ ትንተና/ሐተታ ጀምሮ እንደገና ወደ ታሪኩ ሲመለስ እናያለን፡፡ እንግዲህ ይህ በመሀል የገባ ሐተታ ነው ለተችው ክፍተት ፈጥሮ ነገረ ማርያም የተባለው መጽሐፍ ልዩ ወንጌል ነው ሲሉ በሰፊው የነገረ-ማርያም መጽሐፍ ሊነቅፉ ለጸሐፊው እድል የሰጣቸው፡፡ በትክክልም ይህ በመሀከል የገባው ሐተታ በልዩ ሚስጢራዊ ትርጓሜ ካልሆነ ለጌታ እናት ይነገራል ብዬ እኔም አልቀበለውም፡፡ ግን ይህ የነገረ ማርያም አካል ለመሆኑም ምንም ማሳያ የለም፡፡ እዛ ሐተታ ውስጥ በሌሎቹ የጽኸሑፉ ክፍሎች እንደምናነበው ነገረ ማርያም እንዳለ የሚል ወይም ሌላ መጽሐፍ አንድም ዋቢ ሲጠቀስበት አይታይም፡፡ ጸሐፊው ይህንን ሐተታ መተቸት ወይም ጥያቄ ማቅረብ ቢሞክሩ ሐሳባቸው ከቅንነት የመጣ ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም የተችው አካሄድ ለመቃረንና በድፍረት በአላወቁትም ነገር ወይም ሌሎችን ሆን ብሎ ለማሳሳት እንዳይሆን አሰጋለሁ፡፡ ይህ መሀል የገባ ሀተታ ግን በቤተክርስቲያን ማብራሪያ ሊሰጥበት የሚገባ ጉዳይ ነው በዬ አምናለሁ፡፡
አንድ አንድ ጊዜ መጽሐፍትን የሚበርዙ ነገሮች ልዩ ፍላጎት ባለቸው ተርጓሚዎችና አሳታሚዎች በቅዱሳን መጻሕፍት እንደሚካተቱ እናውቃለን፡፡ ሌላው ቀርቶ ዋናው መጽሐፍ ቅዱስ እንኳን መሠረታዊ ትርጉምን የሚያፋልሱ ብዙ የሚበርዙ ዓረፍተ ነገራት ተካተውበት እናያለን፡፡ ዛሬ ዛሬ እንደውም ይህ መጽሐፍ እየታተመ ያለው እንደየ እምነቱ ፍላጎት ሆኗል፡፡ ይህ የመጽሐፍት በልዩ ታሪክ መበረዝ ደግሞ በሌሎች መጻሕፍትም እንደሚከሰት እራዳለሁ፡፡ ስለ እመቤታችን ዛሬም ድረስ ብዙዎች ሊተነትኑት የሚሞክሩበት አካሄድ መሠረታዊ እውነታዎችን እንዳያፋልስ እሰጋለሁ፡፡ ብዙዎች በሥጋ ዕውቀትና ፍልስፍና እንዲሁም በተራ ስሜት እንጂ በልዑል አምላክ ሀይል ሥር በመንበርከክ በምትመጣ ጥበብ/ፍልስፍናና ማስተዋል ላይጽፉ ይችላሉና፡፡ የሀይማኖትን ነገር ደግሞ ብዙ ሕዝብ የሚቀበለው በየዋሕነት እንጂ ተረድቶና አውቆ አይደለም፡፡ ለክርስትናው ግን የተነገረው መልዕክት እንደ አባብ ብልህ እንደ እርግብ የዋሕ እንጂ የዋህነት ብቻ አይደለም፡፡ ይሄው የዋሕነት በትላልቅ አባቶች ሳይቀር ስለሚያይል ጥፋት እየጠፋ እያዩ እነኳን ተው ብሎ ለመገሰፅ የማይቻለቸው ጊዜ ብዙ ነው፡፡
የጌታ እናት ሩሕሩሕነት በሰው አእምሮ እንኳን ሊታሰብ የማይችል እንደሆን አምናለሁ፡፡ ባሕሪዋ የልጇ በሕሪ ነውና፡፡ ሞትንም የምትፈራው ነች ብዬ አላምንም፡፡ ወዴት እንደምትሄድም ታዋቃለችና፡፡ ይልቁንም ምድራዊ ሕይወቷ ሁሉ የመከራና የሐዘን እንደነበር እናያለን፡፡ ስለብዙዎች እሷ ማዘን ነበረባትና! እንግዲህ በጸሎት መጽሐፍ ነገረ-ማርያም በሚለው ምዕራፍ ውስጥ የገባው ይህ ልዩ ሐተታ እንዴት እንደሆነ አባቶች ቢያብራሩት መልካም ነው፡፡ እንደተባለውም ስሕተት ከሆነ በትክክል በይፋ ተነግሮ መሰረዝ አለበት  ብዬ አምናለሁ፡፡ ስህተት ሆኖ እያለ ቢዘነጋ ግን ራሱ ኑፋቄ ከመሆኑም በላይ ለሌላ ኑፋቄ መዳረጉ ግልጽ ነው፡፡ ነገረ-ማርያምን በድፍኑ ለመንቀፍ ምክነያት እንደሆነ ሁሉ ሌላ የሀይማኖት ጉድፍ እንዳይሆን አስባለሁ፡፡ ብዙዎቻችን በማንበብ እንጂ በማስተዋል የምንሄድ አይደለንምና፡፡ ለፈላስፎቹ ግን አለም አለማትን (the entire universe) በውስጣቸው ያሉትን ሁሉ ፈጥሮ የሚገዛ አምላክ እናት ከመሆን ያለፈ ታርክ አያስፈልጋቸውም፡፡ ለዛም ይመስላል አለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ሰው ሆኖ ሰውን ያዳነበት ጥበቡ/ሚስጢር የሚያስደንቃቸው፡፡ የጌታ እናት ማንነት ታሪክ ደግሞ ያለው አዚህ ልዩ ሚስጢር ውስጥ ነው! 
ቅዱስ አባት ሆይ በማስተዋል አንኖር ዘንድ ከአነት የምትገኝ ዕውቀትን ስጠን!
አሜን!
የታላቋ ቀን ልጅ ሚያዝያ 21፣ 2006 ዓ.ም.

Saturday, April 26, 2014

“አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው”

“አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው”

ከድንበሩ ስዩም
መቀመጫውን ኳታር ያደረገው አልጀዚራ እየተባለ የሚጠራው ቴሌቪዥን ጣቢያ በኢትዮጵያ ላይ ከሰሞኑ አንድ ዶክመንተሪ ፊልም አቅርቦ ነበር። ፊልሙ የሚያተኩረው በሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኘው በአማራ ክልል እና በውስጡ ያሉት ነዋሪዎች በዓይን ሕመም ምክንያት ለዓይነ-ስውርነት እንዴት እንደሚጋለጡ እና ከዚሁ ጋር ተያይዞ ደግሞ በዘመቻ መልክ ወደ ክልሉ ተጉዘው በነፃ የዓይን ሕክምና ስለሚሰጡት ዶክተሮችም የበጎ ተግባር ሥራ ነው። ዶክተሮቹ የበርካታ ሰዎችን ብርሃን መልሰው ሲያመጡትም ፊልሙ ያሳያል። ይህ የዓይነ-ስውርነት በሽታ በክልሉ ውስጥ እጅግ ከመስፋፋቱም በላይ በአጭሩ መፍትሄ ሳይሰጠው ለረጅም ዓመታት ተንሰራፍቶ መቆየቱም በፊልሙ ውስጥ ይተረካል። የዚሁ ክልል ነዋሪዎች የሆኑትም ‘የአማራ’ ህዝቦች ጓዳ እና የኑሮ ደረጃቸውንም የአልጀዚራ ካሜራዎች ለዓለም እያሳዩት ነበር። ከድህነት ጠርዝ በታች የሚኖሩ ሰዎችን ገመና ካሜራዎቹ አልሸሸጉትም ድህነትን ባይተርኩትም እያሳዩን ነበር። ነገር ግን ተረኩት። ተራኪዋም እንዲህ አለች፡- “አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው” በማለት ተናገረች። ነገሩን እንደ ኢትዮጵያዊነት ስንወስደው ልብ ይነካል። ያደማል። ያሳፍራል። ያበሽቃል። ግን ደግሞ በጥሞና ስናስበው ጉዳዩ ያልተጋነነ እውነት ሆኖ እናገኘዋለን። ምክንያቱም አበው ማየት ማመን ነው ስለሚሉ፣ የአልጀዚራ ካሜራዎች እውነቱን እያሳዩን ነበር።
ግን የአማራ ሕዝብ የአፍሪካ ድሃ ነው? የዚህ ሕዝብ ድሕነት እንዴትስ እዚህ ደረጃ ላይ ደረሰ? ቀድሞ እንዴት ነበር? አሁን ምን ሆነ? ወደፊትስ ምን ይሆናል? ብዙ ጥያቄዎችን እያነሳሳን መጫወት እንችላለን። ፊልሙ የለኮሰው የሃሳብ ክብሪት በቀላሉ የሚታለፍ አይደለም።
የአልጄዚራ ዶክመንተሪ በዓይን ሞራ ግርዶሽ እና ተያያዥነት ባላቸው የዓይን ሕመሞች ዙሪያ በጐ ፈቃደኛ ሐኪሞች የሚሰጡትን የዘመቻ ሕክምና እና የሕዝቡንም ኑሮ እያሳየ ነበር። የዓይን የሞራ ግርዶሻቸውን ለማስገፈፍ ከወጣት እስከ አዛውንትነት የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉት ነዋሪዎች ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ በእግራቸው ተጉዘው ሐኪሞቹ ያሉበት ቦታ ሲደርሱና ሕክምናውን ሲያገኙም ይታያል። ለረጅም ዓመታት ብርሃናቸውን አጥተው በጨለማ ሕይወት ውስጥ ሲዳክሩ የነበሩ ሰዎች የብርሃን ፀዳል ሲያዩ የሚፈጠረው ስሜት ልብን ይነካል። አንዳንዱን ደግሞ ሕክምና ቦታም ቢደርስ ዓይኑ በቀላሉ ወደማየት ደረጃ እንደማይደርስና ዓይነ-ስውርነቱ እንደሚቀጥል ሲነገረው ማየትም ልብን ይነካል። ጉዳዩ እጅግ ስሜታዊ ነው። ታዲያ ከዚህ ስሜታዊ ጉዳይ ውስጥ ተፈልቅቆ የሚወጣው ማጠንጠኛ ደግሞ ድህነት ነው።
የዓይነ-ስውርነት ሕመም በስፋት ከተንሰራፋባቸው ክልሎች ዋነኛው የአማራ ክልል ነው። በተለይ ደግሞ ጐጃም ውስጥ ጉዳዩ አሳሳቢ ነው። እኔ ራሴ የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ በአንድ ወቅት ጐጃም ውስጥ የሚገኙ ታላላቅ አድባራትና ገዳማትን ዶክመንተሪ ፊልም ለመስራት በምዘዋወርበት ወቅት በርካታ ሕፃናት፣ ወጣቶችና አዛውንቶች ዓይነ-ስውር ሆነው በማየቴ በእጅጉ ደንግጬ ነበር። ለምሳሌ ዲማ ጊዮርጊስ ተብሎ በሚታወቀው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስትያን የቅኔ እና የሃይማኖት ማስተማሪያ ገዳም ውስጥ ያየሁት ጉዳይ ለዘላለሙ ከህሊናዬ አይጠፋም። በዚያ ገዳም ውስጥ በርካታ ወጣት ተማሪዎች አሉ። ከእነዚህ ተማሪዎች ውስጥ ሲሶው ዓይነ-ስውራን ናቸው። ይሄ ብቻም አይደለም። የእነዚህ ተማሪዎች መምህርት የሆኑት መነኩሴም ዓይነ-ስውር ናቸው። መምህርታቸውም ሆኑ ተማሪዎቹ ዓይነ-ስውራን ነበሩ። ከዚህ በላይ ልብ የሚነካ ነገር የለም። አልጀዚራ ይህን ጉዳይ ግን አልሰራውም።
በወቅቱ የዚህን የዲማ ጊዮርጊስን ጉዳይ በተመለከተ የደብሩን ኃላፊ ጠይቄያቸው ነበር። “ለምንድን ነው ተማሪዎቹም መምህርታቸውም ዓይነ-ስውራን የሆኑት?” አልኳቸው። የደብሩ ኃላፊም ሲመልሱ፤ “ለአብነት (ለቆሎ) ተማሪዎች እንደ ድሮ ምግብ የሚሰጣቸው የለም። ዞረው ለምነው የሚበሉትን አግኝተው መማር አልቻሉም። ስለዚህ ዓይን ያላቸው (ማየት የሚችሉት) ወደ አዲስ አበባ እየሄዱ ሎተሪ ይሸጣሉ። ማየት የማይችሉት እነዚህ ደግሞ የት ይሒዱ? እዚሁ ሆነው ከነችግራቸው እንደምንም ይማራሉ። ዓይነ-ስውራኑ በከፍተኛ ችግር ውስጥ ናቸው” እያሉኝ የደብሩ ኃላፊ አጫወቱኝ።
ጐጃም ውስጥ ለምንድን ነው ዓይነ-ስውርነት የተስፋፋው? ሕፃናት ሳይቀሩ ዓይነ-ስውራን ናቸው። ይህ ጉዳይ ሊመረመር እና መንስኤው ሊታወቅ ግድ ይላል።
አልጀዚራ ዓይነ-ስውርነትን መሠረት አድርጐ “አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ሕዝብ ነው” ብሎ ተናገረ። ይህን አባባል ከሰማ ብዙ ነገር አሰብኩ። እኔ የአማራ ክልል ተወላጅ አይደለሁም። ግን ደግሞ አማራ ኢትዮጵያዊ ነው። ያውም ብዙ ታሪክ ያለው። ብዙ ሀብት ያለው። ባሕል ያለው። ማንነት ያለው። ለሀገሩ ቤዛ የሆነ። ብዙ ነገር መጠቃቀስ ይቻላል። ታዲያ ይህ ህዝብ የአፍሪካ ድሃ ህዝብ ነው ሲባል እንደ ኢትዮጵያዊነት ሁላችንንም ጉዳዩ የሚቆረቁረን ይመስለኛል። ከዚህ ከአልጀዚራ አባባል የሚደሰት ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለኝም። ምክንያቱም ጉዳዩ የአማራ ሕዝብ ብቻ አይደለም። የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጉዳይ ነው።
የአማራ ክልል የአፍሪካ የቋንቋ ማዕከል ነው። በዚህ ክልል ውስጥ ተወልዶ እና አድጐ የመላው ኢትዮጵያ ቋንቋ የሆነው አማርኛ ከአፍሪካ ውስጥ የራሱ ፊደል ያለው ብቸኛ ቋንቋ ነው። በ1950ዎቹ ውስጥ በተሰራ ጥናት የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ መሆን አለበት እየተባለ ሁሉ የሃሳብ ክርክር ቀርቦ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር። ቋንቋው ከመግባቢያነት አልፎ እጅግ የዳበረ የሥነ-ፅሁፍ ቋንቋ ነው። የትልልቅ ፍልስፍናዎችና አመለካከቶች መገለጫም ነው። እናም ይሄ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ፣ ለአፍሪካ ቋንቋንና ሥነ-ጽሁፍን ያበረከተ ነው።
የአማራ ክልል በአፍሪካ ውስጥ ቁጥር አንድ የሆነ የታሪክና የቅርስ ማዕከል ነው። ለምሳሌ የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባሕል ድርጅት /ዩኔስኮ/ የዓለም ድንቅዬ ቅርሶችን እያለ የሚያቆለጳጵሳቸው አያሌ ጉዳዮች መቀመጫቸው እዚሁ አማራ ክልል ውስጥ ነው።
በሰው ልጅ የኪነ-ሕንፃ ምርምር እና ጥናት ውስጥ እስከ አሁን ድረስ የአሰራራቸው ምስጢር ምን እንደሆነ የማይታወቁት የቅዱስ ላሊበላ ፍልፍል አብያተ-ክርስትያናት የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቅርሶች ናቸው።
የ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የዓለም የሥልጣኔ ማዕከል ናት እየተባለች በታሪክ ተመራማሪዎች ዘንድ ዘወትር የምትጠቀሰው የጐንደር ከተማ እና በውስጧ ሰብስባ የያዘችው አብያተ-መንግሥታትና አብያተ-ክርስትያናት የኪነ-ሕንፃ አሰራር የዓለም ድንቅዬ ቅርሶች ናቸው ብሎ የመዘገበው ይሄው የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ነው። ጐንደር በ17ኛውና በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ በጥበብና በስልጣኔ ገናና ሆና በምትጠራበት ወቅት መላው አፍሪካ በባርነት ቀንበር ውስጥ ይዳክር ነበር። በወቅቱ ጥቁር ሕዝቦች ሁሉ በቅኝ ግዛት ተስፋፊዎች መዳፍ ስር ገብተዋል። በጭቆና ውስጥ ለወደቁ ለጥቁር ሕዝቦች በመሉ የነፃነት አርአያ ሆኖ የኖረው ይህ ሕዝብ እና ክልል ዛሬ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ ነው ሲባል ይቆረቁራል። ያማል። ያሳስባል። …. አሜሪካ በእንግሊዞች የቅኝ አገዛዝ ስር ስትማቅቅ ጐንደርን የኢትዮጵያ መዲና አድርጐ ይኖር የበረው አስተዳደር የነፃነት ተምሳሌት ነበር። ዛሬ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ እየተባለ ነው።
በሥነ-ጽሑፍ ዓለም ውስጥም ከአፍሪካ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን 12 ጥንታዊ መፃህፍትን የዓለም ድንቅዬ ቅርሶች ሆነው የተመዘገቡት በዚሁ ክልል የተፃፉና የተገኙ ናቸው።
በሐይማኖት፣ በባሕልና በታሪካዊ እሴቶችም ቢሆን ክልሉ ያበረከተው አስተዋፅኦ ቀላል አይባልም። እንደውም አፍሪካዊ ለዛና ማንነት ያላቸው ጉዳዮችን በስፋት የምናገኝበት ክልል ነው። እጅግ በርካታ ገዳማትና አድባራት እንዲሁም ደግሞ በውስጣቸውም የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ መኩሪያ የሆኑ ቅርሶችን የያዙ ናቸው። ከፍም ሲል ደግሞ የሰው ልጅ ሁሉ መመኪያ የሆኑ ሃይማኖታዊ ቅርሶችን በውስጡ ጠብቆ የኖረ ክልል ነው።
በቅርቡ ዩኔስኮ ከሃይማኖታዊ ክብረ-በአሎች አንዱ የሆነውን የመስቀል አውደዓመትን የዓለም ቅርስ አድርጐ መዝግቦታል። ታዲያ የመስቀል በዓልን እጅግ ብርቅ ካደረጉት ጉዳዮች አንዱ እየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ መስቀል እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም በአማራ ክልል ግሸን ደብረ-ከርቤ ውስጥ መኖሩ ነው። ከዚህም አልፎ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተደጋግሞ የሚጠቀሰው ግዮን /የአባይ ወንዝ/ በወርድና በቁመት ተገማሽሮ የሚገኝበት ቦታ ነው። አባይ የጣና ሐይቅ ማህፀን ውስጥ ገብቶ የሚወጣውም ከዚህ ክልል ነው። ጣና ሐይቅ ላይም 37 ደሴቶች ኖረው ሁሉም ማለት ይቻላል እጅግ ድንቅዬ አብያተ-ክርስትያናት ያሏቸው ናቸው። ያውም ከበርካታ ልዩ ልዩ ቅርሶች ጋር። ታዲያ ይህ ክልል አሁን የአፍሪካ እጅግ ድሃ ህዝቦች መኖሪያ ነው ሲባል ያሳፍራል።
የአማራ ህዝብ ከሌሎቹ የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በመሆን ሀገሩ ኢትዮጵያን ከባዕዳን ወረራ ጠብቆ የኖረ ሀገሪቱ በቅኝ ገዢዎች መዳፍ እንዳትወድቅ መስዋዕትነትን የከፈለ ህዝብ ነው። “የነፃነት – መስዋዕት” በመሆን ሀገሩን አስከብሮ የኖረ የታሪክ ባለቤት ነው። ግን የአፍሪካ ቁጥር አንድ ድሃ እየተባለ ነው።
አማራ ክልል በርካታ የሀገሪቱን ምሁራን ያፈራም ክልል ነው። በሳይንስ፣ በፍልስፍና፣ በታሪክ፣ በቋንቋ እና በሌሎችም የትምህርት መስኮች ውስጥ አንቱ የተባሉ ሰዎችን ያፈራና እያፈራም የሚገኝ ነው። ግን ድሃ ህዝብ ነው። ኧረ ሌሎችንም ጉዳዮች እያነሳሳን መጫወት እንችላለን። ቢሆንም እዚህ ላይ ቆም እናድርገውና ድህነት ምንድን ነው? ለምንስ የአፍሪካ ድሃ ሕዝብ ሆነ የሚለውን ሁላችንም መልስ ለመስጠት መሞከር አለብን።
ይህ ሕዝብ በአንዳንድ መስመር በሳቱ ግለሰቦችና ተቋማት አማካይነት ‘አድሃሪ’፣ ‘ትምክተኛ’፣ ‘ነፍጠኛ’ ወዘተ እየተባለ የራሱ ወገኖች በሆኑ ኢትዮጵያዊያንም ሲንጓጠጥ እና ሲዘለፍ የኖረም ነው። ይሄ ደግሞ ማኅበራዊ መሸማቀቅን ፈጥሮበታል። በእነዚህ ቅስም ሰባሪ ቃላት እንደልባቸው ሲዘልፉት የነበሩት ሰዎች አንድም ቀን ሲጠየቁ እና የሚናገሩትም ነገር ስህተት እንደሆነ በአደባባይ ተነግሯቸው አያውቅም። ይሄ ሲዘለፍ የኖረው ህዝብ አሁን ደግሞ የአፍሪካ ቁጥር አንድ ድሃ ሆኗል። ኦነግን የመሳሰሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የማሸማቀቁን ሚና በሰፊው ተጫውተውታል።
ሌላውና አንገብጋቢው ነገር ደግሞ የአማራ ህዝብ ራሱን መጠየቅ አለበት። የዚህ ሁሉ ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስ፣ ማንነት ባለቤት ሆኜ ለምን ድሃ ሆንኩ ብሎ መጠየቅ ያለበትም ወቅት ነው። በርግጥ ይህን ጥያቄ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊጠይቀው የሚገባ ነው። ለምን ድሃ ሆንን?
አልጀዚራ የአማራን ህዝብ የአፍሪካ ቁጥር አንድ ድሃ ነው ቢለው ያበሽቃል እንጂ ሀሰት አይደለም። የአማራ ህዝብ በተለያዩ ከተሞች ውስጥ በልመና የሚተዳደር ነው። በሰው ቤት ሰራተኝነት የሚያገለግሉት የአማራ ተወላጆች ናቸው። ከቦታ ቦታ የሚሰደዱትም የሚፈናቀሉትም እነርሱ ናቸው። ግን እንደ አንድ ህዝብ የተሻለ ህዝብ እንዲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለው ጥያቄም መመለስ አለበት።
በባሕል፣ በታሪክ፣ በቅርስ ወዘተ መበልፀግ እንዴት ከድህነት ሊያወጣን አልቻለም ብሎ ማሰብም ተገቢ ነው። በአጠቃላይ ሲታይ ኢትዮጵያ ከድህነት ወለል በታች ናት እየተባለ በሚነገርበት ሁኔታ ውስጥ የአማራ ህዝብ ደግሞ የድህነት ጣሪያው የጐላ መሆኑን አልጀዚራ ተናግሯል፤ ስለዚህ ቆም ብለን ረጅሙን ጉዞ ከአሁኑ አሻግረን እያየን መጪውን ጊዜ የተሻለ ለማድረግ ብዙ መጣር አለብን።
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

Monday, April 21, 2014

ኢትዮጵያን ለዘመናት የተቆራኛት ልክፍት፡ ከዓላማ ይልቅ ጥላቻን መሪ ያደረገ ፖለቲካ!




እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል አደረሳሁ!
ይህ የእኔ ብቻ አመለካከት ነው ብዬ አላምንም፡፡ እንደ እኔ አረዳድ ኢትዮጵያ እጅግ ብዙ ዘመናት ለትውልድና አገር በማያስቡ መሪዎች የተመራች እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ማመን ብቻም ሳይሆን ምንአልባትም ማንም ምሁር ነኝ የሚል ሳይቀር አደለም ብሎ ማሳመኛ ማቅረብ በማይችልበት መልኩ የታሪክ እውነታዎቹ ለእምነቴ ዋቢ ሆነው ይቆሙልኛል፡፡ ዛሬ የምናያት ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር ታላቁ ሰው ምኒሊክ ከመመስረታቸውም በፊት በሌላ ሥምም ቢሆን የዛሬይቱ ኢትዮጵያ አካል የሆነው ታሪክ በዓለማችን ካሉ ጥንታዊ ከሚባሉ አገራት አንዷ ያደርጋታል፡፡አክሱማውያንና በአገዋውያን (ዛግዌያውያን) የነበሩ የታሪክ ምስክሮቿ ብልህና አስተዋይ መሪዎች እንደነበሯት የሚያሳየውን ያህል ከዚያ በኋላ የመጡ መሪዎቿ በጣም የወረደና አሳፋሪ አስተሳሰብ እንደነበራቸው እንገነዘባለን፡፡ እርግጥ በቀደሙት የአክሱማውያን ወይም ዛግዌያውያንም ዘመን ምን ያህሉ ዘመናት በአስተዋይ መሪዎች ምንያህሉ ደግም በወራዳ መሪዎች እንዳለፈ አላውቅም፡፡ ሆኖም ተደምሮና ተቀንሶ ውጤቱ የአስተዋይ መሪዎቹ ዘመናትና ሥራዎች እንደሚመዝን እረዳለሁ፡፡

ከአገዋውያኑ በኋላ ግን በግልጽ የሚታይ ከመንደር ያለፈ አስተሳሰብ ባልነበራቸው የዱርዬነት ባሕሪ በነበራቸው አለሌ መሪ ተብዬዎች ታላቁ ባለራዕይ ምኒልክ አንድ አስከሚያደርጓት ድረስ አገሪቱ ተበታትና እንደነበር ሁላችንም እናውቃለን፡፡ የታላቁ ባለራዕይ ምኒልክ ምኞትና ቁርጠኝነት አገሪቱን ወደ ትልቅነት መስመር ላይ ሊያመጣ ቢችልም ባለራዕዩ በዘመናቸው ከነበረባቸው የማየሕይብ ከሰፈርና ከራሳቸው ሆድ በላይ ማሰብ ከማችሉ ሰዎች ጫና በተጨማሪ ለሕይወታቸው ሕልፈት ሳይቀር የክፉ ሰዎች መሠሪ እጅ እንደነበረበት ይነገራል፡፡  የምንሊክ የሥልጣን ሂደት ሁሉ ግን በተቀናቃኞቻቸው ላይ መሠሪ በመሆን አልነበረም፡፡ ይህ በአለፈው ከአነሳሁት አገርን አንድ የማድረግ ጦርነቶች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ ምኒልክ ከእሳቸው በፊት ለነበሩት ለዮሐንስም ሆነ ለአሳዳጊያቸው ግን ሊያጠፏቸው ለሚፈልጓቸው ቴዎድሮስ መጥፋት ምክነያት አይደሉም፡፡ እንደውም የቴዎድሮስን ሞት ሌሎች አንደምስራች ሲነግሯቸው እሳቸው የመረረ ሐዘን ውስጥ እንደገቡ ይነገራል፡፡ በቴዎድሮስም ላይ እንዲያምጹ እንግሊዞቹ ሲጎተጉቷቸው የቱንም ያህል ሊያጠፋኝ የሚፈልገኝ ጠላቴ ቢሆንም እጄን በእሱ ላይ አነሳ ዘንድ ከጠላቶቹ ጋር በጠላትነት በአሳዳጊዬ ላይ ለመተባበር አይቻለኝም ያሉ ናቸው፡፡ በተቃራኒው ለቴዎድሮስ መጥፋት ዮሐንስ ከእንግሊዞቹ  ጋር እንደተባበሩ ይነገራል፡፡ ሆኖም ዮሐንስ በመታልል ነበር እንጂ በአገር ላይ በነበራቸው አመለካከት እንዳለነበር ብዙዎች ይናገራሉ፡፡ ምኒልክ ከዮሐንስ ጋር በነበራቸው ሥልጣን ሽኩቻ አቅሙና የተመቻቹ ሆኔታዎች ቢኖራቸውም ዮሐንስን በማጥፋት ሥልጣን መያዝን አልፈለጉም፡፡  በዚህ ሁሉ ትግስታቸውና በጎ አመለካከታቸው እግዚአብሔር ለእኚህ ሰው ይችን አገር ይገነቧት ዘንድ  ሥልጣንን አሳልፎ እንደሰጣቸው እረዳለሁ፡፡
   
ከዚህ ዘመን ሀኋላ ስናይ የኢትዮጵያ የስልጣን ሽግግር እንትና እንትናን ገደለ፣ እንትና እንትናት ከስልጣን አወረደ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ምኒልክ ወንድ ልጅ ስላልነበራቸው የልጅ ልጃቸው ኢያሱን እንደመረጡ ይነገራል፡፡ ልብ እንበል ኢያሱ ብዙዎች ለመካድ የማይችሉት የምኒልክ አይነት ራዕይ እንደነበራቸው ታሪክ ይናገራል፡፡ ምኒልክ የኢያሱ የጭቅላነት እድሜ እንኳን ሳይከልላቸው ሊተካቸው የሚችለውን ሰው ለመምረጥ ችለው ነበር፡፡  ሆኖም የኢያሱን ልጅነታቸውንና ከልጅነት ጋር የተያያዙ ባሕሪያቸውን እንደምክነያት አድርገው መሠሪዎቹ ኢያሱንና የምኒልክን ራዕይ ለማጥፋት መሴራቸውን ቀጠሉ፡፡ ኢያሱንም በእንጭጩ አስቀሯቸው፡፡ በምትካቸው የምኒልክ ልጅ የሆኑት ዘውዲቱ መጡ፡፡ ዘውዲቱ በአገር የመምራት አቅምና አስተዎሎታቸው ምን ያህል እንደነበር ባላውቅም እሳቸውም ቢሆኑ በሴረኞቹ ጠፉ፡፡ አገሪቷን ለብዙ ዘመን ለመምራት እድል የገጠማቸው ኃ/ሥላሴ ተተኩ፣ እሳቸውም ያው ዕጣ ገጠማቸው፣ በደርግና በንጉሱ መካከል ብዙ ጥሎ ማለፎች ተካሄዱ ደርግ መጣ ሁሉንም ይውደም እያለ አወደመው፡፡ የደርግ መሪ የነበሩት መንግስቱ የሞት ዕጣ ባይገጥማቸውም ሌሎች ብዙ ባለስልጣናት የዛሬውን መንግስት በመሠረቱ ቡድኖች በነው ጠፉ፡፡ አሁንም ይህ ሂደት አላባራም እንደ ቀጠለ ነው፡፡

ከምኒልክና ከልጅ ልጃቸው ኢያሱ በቀር ከዚያ በኋላ በመጡት መሪዎች ሁሉ መሠሪነትና አልፎም በእጃቸው ደም እንዳለ እረዳለሁ፡፡ ከሁሉ የከፋ አደገኛ ትውልድ ግን የሚባለው ያ የንጉሳውያኑን ስልጣን አስወገድኩ የሚለው ትውልድ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ እስካሁንም ያ ትውልድ ለዚች አገር የጥፋት ማሕደር እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ያ ትውልድ የሕዝብ ሕመም የማይሰማው ጥላቻ የለከፈው ውጤታማነትን ሁልጊዜ ሌላውን ተቀናቃኝ ብሎ የሚያምነውን በማጥፋት ብቻ ጋር የሚያቆራኝ፣ ሐይማኖትና ማንነትን የሚገልጽ ባሕል የሌለው የነወረ ትውልድ እንደሆነ አስባለሁ፡፡ ያ ትውልድ ግን ራሱን የለውጥ ሐዋሪያ እንደሆነ አድርጎ ዛሬም ድረስ ይነግረናል፡፡ አሁንም ብዙ በመርዝ የተለወሱ አስተሳሰቦችን ይመግበናል፡፡ እንግዲህ ዛሬ በሥልጣን ላይ ያለው መንግስት መሪዎችም ሆኑ ተቃዋሚ ነን የሚሉ በተለያዩ አገራትና አገር ቤትም ያሉ ቡድኖች መሪዎች በዋነኝነት የዚያ ትውልድ "በረከቶች" እንደሆኑ እናስተውል፡፡ እነዚህ ሰዎች የሥልጣንና የግል ፍላጎት ጥማት እንጂ የአገራዊ አላማና ራዕይ ተቀናቃኞች እንዳልሆኑም እንረዳለን፡፡ ስለሆነም የእነሱ ሥልጣናቸውንና የግል ጥማታቸውን የሚያሳካላቸው ከሆነ የቱንም ያህል የሕዝብንና የአገርን ጥፋት የሚያስከትል አካሄድ ትክክል እንደሆነ ያምናሉ ብዬ አምናለሁ፡፡

ከላይ በመግቢያነት ያነሳኋቸው ጉዳዮች በዝርዝር ለማስተዋል እንዲረዳን ያቀረብኩበት ምክነያት የግንቦት 7 የሚባለው ቡድን ሰሞኑን ያስነበን "ይድረስ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት" በሚል ያወጣው ጽሑፍ ነው፡፡ ሲጀምር ጽሑፉ ያው እንደተለመደው ኃላፊነት የጎደለውን የጥፋት ዜማ ሊያስነበበን ተፍጨረጨረ እንጂ በበሳል አቀራረብ እንኳን የቀረበ አይደለም፡፡ እርግጥ ጉልበትኝነትና ቂመኝነት እንጂ ማስተዋልና በሳልነት ያ ትውልድ በምለው ብዙም ባሕሪው አይደለም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ አንድ ባለስልጣን ስላቀረበው ሪፖርት ማግዘፍና አቅራቢውን ግለሰብ ባለስልጣን ተራ ስድብ በመሳደብ አገራዊ ራዕይና አላማ ያለው ድርጅት ነኝ የሚል ሕዝብን ለመማረክ መሞከር አለመብሰል ነው፡፡ የከፋው ግን ከራስ ፍላጎትና ጥቅም ባለፈ የአገርና የሕዝብ ጥፋት ጉዳዩ እንዳልሆነ የሚያሳየው የሐገርን መከላከያ ሰራዊት መሳሪያህን በባለስልጣናት ላይ አዙር የሚለው ጥሪው ነው፡፡

በእኔ ግንዛቤ የአገር መከላከያ ሠራዊት የጠበቀ ሥርዓታዊ አወቃቀር፣ የአዛዥና ታዛዥ አስተዳደር በጽኑ የሚከበርበት ተቋም ነው፡፡ ይህ ደግም ለኢትዮጵያ የተለየ ሳይሆን በሁሉም ሀገራት ያለ የተቋሙ መዋቅራዊ ባሕሪ ነው፡፡ የዚያንው ያሕል የዚህ አደረጃጀት ማላላትና አንዱ በአንዱ ላይ ማመጽን የሚፈጥር ክፍተት ከፍተኛ ጥፋትንና ለአገር ውድመት ሳይቀር አደጋን የሚያስከትል ነው፡፡ ይህ ተቋም እጁ ያለው አውዳሚ ግን ጠላትን ለመከላከል ታስበው የተዘጋጁ የጦር መሳሪያዎችን እንጂ ዳቦና ኬክ አይደሉም፡፡ እንጊዲህ እንዲህ ያለው ተቋም አባላት መካከል አለመግባባትና ወደጦርነት የሚያመራ ግጭት ቢፈጠር ውጤቱ ምን እንደሆነ እናስተውል፡፡ ይበልጠውንም ተቋሙን በሚመሩት ላይ ሠራዊቱ ቢያምፅ ማን እየመራው ሊቀሳቀስ እንደሚችል አስቡት! አነሰም በዛም፣ ወደድናቸውም ጠላናቸውም ዛሬ የኢትዮጵያን መከላከያ ሠራዊት የሚመሩት ሥልጣን ላይ ያለው መንግስት ባለስልጣናት ናቸው፡፡ አነሰም በዛም፣ ወደድናቸውም ጠላናቸውም አገሪቱንም አየመሩ ያሉት እነዚሁ ባለሥልጣናት ናቸው፡፡ የእነዚህ ባለሥልጣኖች በመልዕክቱ እንደተላለፈው በሠራዊቱ አባላት መጥፋት አገሪቷን ወዴት ሊወስዳት እንደሚችል ማሰብን አንዴት አለተቻለውም ግንቦት 7 የሚባለው ቡድን ወይም በግልም ከሆን የጽሑፉ አቀራቢ፡፡ መልዕክቱስ እውን ሠራዊቱ እየደረሰበት ስላለው አድልዖና በደል በመቆርቆር ነው ወይስ ዛሬ ባሉት የአገሪቱ ባለስልጣናት ላይ ስላለው ጥላቻና የእራስንም ፍላጎት ለማሳካት በሚል እሳቤ ብቻ  አገርና ሕዝብ ምኔ ነው በሚል ለጥፋት መዘጋጀት፡፡

በኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር ቀረበ የተባለው ሪፖርት ታይተዋል በተባሉት የቤሕረሰብን ስብጥር የሚያሳዩ የሠራዊት ብዛት በዛው ልክ የሠራዊቱን አመራር ሥብጥር ያሳያል ማለት እንደሆነ ብዙዎቻችን እናውቃለን፡፡ እንደ አዲስ ነገር የዚህን ሪፖርት መልዕክትና ግድፈት ማሳየትም አያስፈልገንም፡፡ የሪፖርቱን ግድፈትና ደካማነትስ እንደ ልዩ የገዥው ፓርቲ ማሳያ አድርጎ ማቅረቡ ምን ያህል የበሰለ ነው?  በብዙ ተቋማት የቤሕር ተዋፅዖ አለመመጣጠን እንዳለ እናውቃለን፡፡ መፍትሔ ግን ግደለው ፍለጠው ነው? ወይንስ ሰዎችንም ይሁን ቡድኖችን ወደትክክለኛ አመለካከት ማምጣት? ደግሞስ ማንን ነው የምንገድለው? የማን ወገን ሟች የማን ወገን ገዳይ ነው የሚሆነው?! ሲጀምር እኔ በብሔረሰብ ማንነት አላምንም፡፡ ብዙው ራሱ በፈጠረው ማንነት ሊያምን ይችላል፡፡ እኔ ግን ማንንም የሚወክል ብሔረሰብ የለኝም፡፡ ኢትዮጵያዊነቴ አላነሰኝም፡፡  ወደድኩም ጠላሁም ግን የዚሁ የዘር ማንነት ችግሮች ሰለባ በሆኔ አልቀረም፡፡ መቼም ቢሆን ግን በሌላው ላይ ጥላቻን ለማስተናገድ አእምሮዬ ፍቃደኛ የሚሆን አይመስለኝም፡፡ ሌሎች ለራሳቸው የኑሮ መደላደልና ጥቅም የፈጠሩት የማንነት መመንዘር ሴራ ብዙዎቻችን ተገዥ መሆናችን ሳያንስ እኛው እየረገምን እኛው የዚሁ ሴራ ዋና አዛማች ስንሆን አዝናለሁ፡፡ ትክክለኛው አመለካከት ግን ብዙም የዚያን ያህል የማደንቀው ሰውም ባይሆን ብዙዎች ባሕሪው ነው ሰዎችን ከጥላቻ ይልቅ በፍቅር ለማሸነፍ አቅም ነበረው የተባለው የደቡብ አፍሪካዊው ማንዴላን ማሰብ ጥሩ ነው፡፡ እኔ የሚገባኝ ምኒልክ ከማንም በላይ የዚህ ባሕሪ ባለቤት ቢሆንም ብዙዎቻችሁ ዘንድ የማታምኑበት ስለሆነ ነው ማንዴላን ማንሳቴ፡፡

እንግዲህ የግንቦት ሰባትም ይሁን ሌላ ቡድን ወይ አባል ጥላቻን እየሰበከ እሱ በተራው ሥልጣን ቢይዝ ለዚያ ዛሬ ጠላቻውን በሚነገረን ሕዝብም ይሁን ግለሰብ ላይ በቀሉ ምን ሊሆን ነው?! የብሔረሰብ ሥም መጥራት ስላልፈለግሁ ነው ግን እርግማን ሆኖብን ፌደራላዊ አወቃቀራችንም፣ ዛሬ ሥልጣን ላይ ያለው መንግስት የቡድን ስብስብ (ፓርቲዎች)ም በዘር መሠረት ላይ የተደራጁ ናቸው፡፡ ብዙ ተቃዋሚዎችም እንዲሁ ናቸው፡፡ በግልጽ ሥማቸውን የዘር ከአደረጉት በተጨማሪ ብሔራዊ ነን የሚሉ የአገሪቱን ሥም በሥማቸው ያስገቡትን ጨምሮ ሌሎች ሥሞችን የመረጡ ቡድኖች ሁሉ ከዚህ ከዘር ልክፍት የጸዱ ለመሆናቸው ምንም ማሳያ የለም፡፡ እናስተውል ብዙዎቹ መሪዎቻቸው የዚያ የብሔር(ዘር) ጥያቄ እመልሳለሁ በሚል ዘረኝነትን የወለደው ትውልድ መሆናቸውንም አንዘንጋ፡፡ ከዚህ ቢተርፉም የዚያው ትውልድ ልዩ መገለጫው በሆነው ውጤታማነትን ለማሳካት ተቀናቃኝህን አጥፋ (Eliminate your competitor) የሚል ፍልስፍና ልክፍት የተጠናወታቸው እንደሆኑ እናስተውል፡፡ እድል ሆኖ የዛሬውም ትውልድ ከእነሱ በቀልን የተማረ እንጂ ምህረትንና ሰብዐዊ ክብርን የተላበሰ ሊሆን አልቻለም፡፡ የጥላቻ በአመረቀዘው አእምሮ ራስወዳድነት በተጠናወተው ሕሊና አገርንና ሕዝብን የሚወክል መሪ ማግኘት አይቻልም፡፡ማንም አገር መምራትን የሚፈልግ ቡድን ወይም ግለሰብ ለሁሉም እኩል የሆን ንጉሳዊ (Royal) ልብ ሊኖረው ይገባል፡፡ በሳልና ከጥላቻ የነጹ አእምሮዎች አሸናፊነታቸው የሰፋ ነው፡፡ ግደለው ፍለጠው አብቅቶ የአንዱ ውድቀት ለሌላው እንደ ስኬት የሚታሰብበት ዘመን አብቅቶ መሠረታዊ የሰብዓዊ ማንነት ተምሳሌት እንሆን ዘንድ አመኛለሁ፡፡ ጥንታዊያኖቹ ክርስቲያን የነበሩት መሪዎች ከሌላ አገር የመጡ በሐይማኖትም የመልክም የማይመሳሰሏቸውን አረብ ሙስሊሞች ሲቀበሉ መሠረታዊ ፍልስፍናቸው ሰው መሆናቸው እንጂ የዘር ወይም የሐይማኖት ማንነታቸው እንደልሆነ እንረዳለን፡፡  ዛሬ በብዙ አለፍንባቸው ዘመናት የተነሱ ወራዳ መሪ ተብዬ ምክነያት በመጣብን ድህነት ምክነያት የሚያደምጠን አጥተን ሌሎች ስለ ስብዕናና መልካም አስተዳደር ሊያስተምሩን ቢሞክሩም አሁንም ቢሆን ከማንም በተሻለ ሰበዓዊነትና መልካም አስተዳደርን ለመፍጠር በሕሎቻችንና የማሕበራዊ ፍልስፊናዎቻችን ጥሩ አጋጣሚዎች እንደሆኑ አምናለሁ፡፡ ግን እየዘገየን በሄድን ቁጥር ሁሉም ደብዛው ጠፍቶ ማንነቱን ያለወቀ ሌላ ትውልድ እየመጣብን እንደሆነ እሰጋለሁ፡፡ ያ አብዮት አምጥቻለሁ የሚለው ጥላቻን ከብቃት ያልለየው ትውልድ ግን ዝም ይበል እሱ ደም የተለወሰ እጅ አለውና፡፡   

እግዚአብሔር ሆይ የቅርታን የሚያደርግ ለሕዝብና አገር አሳቢ መሪ ስጠን! አሜን!

የታላቋ ቀን ልጅ ሚያዝያ13 2006 ዓ.ም

Friday, April 18, 2014

ይድረስ ለብዙሃኑ የሠራዊቱ አባል ወገናችን!!

ይድረስ ለብዙሃኑ የሠራዊቱ አባል ወገናችን!!

Weekly_Editorial_Tumbnailየመከላከያ ሚኒስትር በተሰኘው የውሸት ሥልጣን ላይ የተቀመጠው አድርባይ ሲራጅ ፈርጌሳ ለይስሙላው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፓርት፣ “የመከላከያ ሚኒስትር የብሔር ተዋጽዖ የተመጣጠነ” እንደሆነ ገለፀ። እንደ ሰውየው ሪፓርት ከሆነ የመከላከያ ሠራዊቱ 29.46 በመቶ አማራ፣ 25.05 በመቶው ከደቡብ ብሔሮች የተውጣጣ፣ 24.45 በመቶ ኦሮሞ፣ 17.47 በመቶው ትግራይ እና የተቀሩት ክልሎች ድርሻ 4.17 በመቶ ነው። መረጃው የተቀናበረው በክልል ቢሆንም የቀረበው ግን በዘር ነው። “ተመጣጠነ” የተባለውም የክልሎች ተዋጽዖ ሳይሆን የዘር ተዋጽዖ ነው። ሠራዊቱን እንዲህ በዘር ሸንሽንኖ የስታትስቲክስ ጨዋታ መጫወት አሳዛኝም አሳሳቢም ነገር ነው። የሆነ ሆኖ ይህ መረጃ፣ መረጃ ነው ተብሎ ለሕዝብ ቀርቧል።
ይህንን መረጃ የሰማ ማሰብ የሚችል አዕምሮ ያለው ሰው የሚጠይቀው የመጀመሪያ ጥያቄ “የሠራዊቱ ስብጥር በተገለፀበት ዓይነት የመኮንኖቹም ስብጥር ለምን አልተገለፀም?” የሚል ነው። ይህ ጥያቄ በአስተዋይ ሰው አዕምሮ ውስጥ በተነሳነበት ፍጥነት ምላሽ ያገኛል፤ ምክንያቱም ምላሹ እዚያው እቁጥሮቹ ውስጥ አለ። የመኮንኖቹ ስብጥር ያልተነገረበት ምክንያት አብዛኞቹ መኮንኖች በ17.47 በመቶው በመሆናቸው ነው። ወደዚህ መምደሚያ የሚደርሰው አሳቢው ስለፈለገው ሳይሆን የመረጃው አቀራረብ አመክኖ (ሎጂክ) ወደዚያ ስለሚገፋ ነው። በዚህም ምክንያት በሲራጅ ፈርጌሳ አንባቢነት የቀረበው የህወሓት ሪፓርት በገዛ ራሱ ላይ ነው የተኮሰውም።
እኛ እንደ ሲራጅ ፈርጌሳ የዘር ስታትስቲክስ ውስጥ አንገባም፤ መልዕክታችን ለተገፋውና እየተበደለ ላለው ለመላው የሠራዊቱ አባል ነው።
ይድረስ ሹመትና ኃላፊነት ተነፈገህ፤ የጥቂቶቹን ሀብትና ዝና ጠባቂ እንድትሆን ለተፈረደብህ ወገናችን!!! እስከመቼ ለህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ መኮንኖች ባርነት ትገዛለህ? ይህ ውርደትህ የሚያበቃው መቼ ነው? የታጠቀው መሣሪያ የአገርህና የራስህ ክብር ማስጠበቂያ፤ ነፃነትህን መጎናፀፊያ የምታደርገው መቼ ነው? ለመሆኑ ለመኮንንነት የሚያበቃ ጭንቅላት፣ ልምድ ወይም እውቀት ከፓርቲ አባልነት ነው የሚገኘው? ህወሓቶችና አጋሮቻቸው በሠራዊቱ ያሉትን ቁልፍ ኃላፊነቶችን ሁሉ ጠቅልለው ይዘው “ጀሌዎቻችን እንዲሆኑ ፈቅደንላቸዋል” የሚል ሪፓርት የሚያቀርቡት ምንኛ ቢንቁን ነው? ይህንን ውርደት ኢትዮጵያዊው ወኔህ እንዴት ይቀበለዋል?
ኢትዮጵያዊው ወታደር ከሌላው ኢትዮጵያዊ በባሰ በአምባገነንና ዘረኛ አለቆቹ እየተዋረደ እንደሆነ በገሃድ የሚታይ ጉዳይ ነው። የህወሓት አባላት ቁልፍ የስልጣን ቦታዎችን ይዘው ጦር ሠራዊቱን እንደ ፓርቲ መዋቅር ሲመሩት ማየት የሠራዊቱን አባላት ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያንገበግብ ጉዳይ ነው። ሠራዊቱ አገርና ሕዝብን ሊጠብቅበት ይገባ የነገረው መሣሪያ በንጹሃን ዜጎች ላይ እንዲያነሳ፤ ሰላማዊ ሰዎችን እንዲደበድብ፣ እንዲረግጥና እንዲገድል የሚያዙት እነዚህ የህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ አለቆቹ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃል። ሆኖም የኢትዮጵያ ወታደር የታዘዘው ሁሉ የሚፈጽም ባርያ አይደለምና በእነዚህ ጥቂት ዘረኛ አለቆችህ ላይ እንዲነሳ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠይቃል።
ውድ የኢትዮጵያ ወታደር ሆይ!!! “ዘረኛነት በቃኝ” በል። ለነፃነት፤ ለእኩልነት፤ ለአገር ክብር በሚታገሉ ወገኖችህ ላይ ክንድህን አታንሳ። የጥቂት ዘረኞችን ሥልጣን በማራዘም ከሚመካብክ የኢትዮጵያ ድሃ ሕዝብ ጋር ዘላቂ ቂም ውስጥ አትግባ። በትእቢት “ሁልሽንም ረግጠን እንገዛለን” ብለው የሚፎክሩት አንተን ከወገንህ ጋር ደም በማቃባት ነውና “እምቢ!” በላቸው። ለዘረኞች ስልጣን ብለህ አትሙት! እንዲያውም ለገዛ ራስህ ክብር፣ ለቤተሰቦችህና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነት ግንባር ቀደም አርበኛ ሁን።
ከላይ የተባለው ለፓሊስ አባላትም ይሠራል። በህወሓትና ህወሓት በየቦታው በፈጠራቸው ጀሌዎች የሚመራ በመሆኑ ከሕዝብ ፍላጎት በተፃፃሪ የቆመ ይምሰል እንጂ የኢትዮጵያ ፓሊስ የሕዝብ ወገን እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍትህ እጦት የሚሰቃየውን ያህል ብዙሃኑ ፓሊስ በፍትህ እጦት እየተሰቃየ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኑሮ ጫና እንዳዳከመው ሁሉ የኢትዮጵያ ፓሊስም ኑሮ ከብዶታል። እንደሌላው ሰው ሁሉ ፓሊስንም ዘረኝነት አስመርሮታል። ብዙሃኑ ፓሊስ አቅሙን በጥቂት አምባገነን አለቆቹ ላይ የሚፈትሽበት ጊዜ ደርሷል።
የስለላ ተቋማቱ ጉዳይ ለየት ይላል። “ደህንነት” ተብሎ በሚሞካሸው የጆሮጠቢዎች ስብስብ በሆነው መሥሪያቤት እና በኤክትሮኒክስ ብርበራ የተሠማሩ “ባለሙያ ጆሮ ጠቢዎች” ውስጥ ህወሓት በአለቃነትም በምንዝርነትም አብዛኛውን ቦታ ይዟል። ሆኖም እዚህም የሕዝብ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃሉ። በእነዚህ ቦታዎች ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ሲቻል በገሃድ ሳይቻል በሚስጥር ተቋማቱን የማዳከም ሥራችዎችን መሥራት የህሊናና የዜግነት ግዴታችሁ ነው። ከእናንተ ብዙ፤ እጅግ ብዙ ይጠበቃል። የምታሾልኳት ትንሿ መረጃ የብዙዎችን ሕይወት ልትታደግ ትችላለች፡
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት የጦር፣ የፓሊስና የስለላ መዋቅሮች ውስጥ የሕዝብ ወገኖች እንዳሉ ያውቃል። እነዚህ ወገኖቻችን እንደሌላው ሕዝብ ሁሉ – አንዳንዴም ከሌላው በባሰ ሁኔታ – በፍትህ እጦት፣ በኑሮ መክበድና በዘረኝነት እየተሰቃዩ መሆናቸው ያውቃል። እነዚህ ወገኖቻችን ጥለው እንዲወጡ፤ ይህ ካልተቻለም ከውስጥ ሆነው የወያኔን የጦር፣ የፓሊስና የስለላ መዋቅሮች እንዲያፈራርሱ ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

Wednesday, April 9, 2014

ኦሮሞ ነኝ የሚለው ብዙው ሕዝብ በታላቁ ኢትዮጵያዊ ሚንሊክ ላይ ያለው ጥላቻ ከምን የመጣ ነው?


እጅግ ክፉና ማንነትን ከሚያዋርዱ ነገሮች አንዱ አእምሮን ከእውነትና ማስተዋል አስርቦ መነሻው ምን እንደሆነ ብዙዎች በማያውቁት ስሜተኝነት መነዳት ነው፡፡ ይን የሰው ልጆችን በስሜተኝነት የመጥለፍ አጋጣሚን ለመፍጠርና በተፈጠረውም አጋጣሚ ራሳቸውን አግዝፈው የሚኖሩ ግን በተፈጥሮ ብስለታቸው የወረዱ ሌሎችንም በእነሱ ደረጃ ከእነሱም ባነሰ ሊያዋርዱ ሌሊት ከቀን እንቅልፉ የሌላቸው ከዚያም በላይ በዕርኩሳን መናፍስት የሚታገዙ ሰብዐዊ ፍጡሮች በዙሪያችን እንደሚያንዣብቡ ብዙዎቻችን አንረዳም፡፡ እንደነዚህ ያሉ ሰዎች አእምሮአቸው በጎ እንዳያስብ የነጠፈና  በምትኩ ክፋትን ከቀን ወደቀን በማሳደግ ራሱን ሰይጣንን የሚተካ ባሕሪን ያዳበሩ ናቸው፡፡  በዚህ አደገኛን በመረቀዘ አእምሮአቸው ሌሎችን የመርዛሉ ያጠፋሉ፡፡ እነዚህ ሰው የሚመስሉ ግን በአካል የሚንቀሳቀሱ ሰይጣኖች ከሚበዙባቸው ቦታዎች ደግሞ ሕዝብ ትላልቅና የተከበሩ ብሎ በሚያስብባቸው ከፍተኛ አመኔታ በሚሰጣቸው ነው፡፡ ከነዚህም ውስጥ የፖለቲካ የሥልጣን መዋቅሮችና የሐይማኖት ተቋሞች ቀዳሚውን ቦታ ይይዛሉ፡፡
ከላይ የተጠቀሱት ሁለቱ መዋቅሮች ባሉ መሪዎች ላይ ሰዎች ከፍተኛ አመኔታን ይሰጣሉ፡፡ ግን ብዙ ጊዜ ለአመኔታቸው አጸፋው መልካም ነገር ላይሆን ይችላል፡፡ ብዙም ጊዜ ወድቀትና ወርደት ይሆናል፡፡ ሁለቱም መዋቅሮች እጅግ የበሰለ አእምሮን፣ ቅንነትን፣ የሕዝብ እንደራሴ መሆንን የሚጠይቁ ቢሆም በብዙ የታሪክ ገጠመኞች ግን ተቃራኒው ሲሆን ይስተዋላል፡፡ በአሁን ዘመን ደግሞ ከመቼውም የከፋ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ እነዚህ ከላይ የተጣለውን ሰይጣን የሚወክሉ ሰብዓዊ ፍጥረቶች በቅንነትና በበሰለ አእምሮ ለሕዝብና ለአገር ክብር የነበሩ ሰዎች ታሪካቸው እንዳይታወቅ፣ ከታወቀም ራሳቸው በፈጠሩት ሌላ ታሪክ የእነዚህን ባለታሪኮች ታሪክ በማጉደፍና የቀደመ ታሪክን የማያውቅ ሌላ እነሱን የመሰለ ትውልድ ተክቶ የታላላቅ ባለራዕዮችን ታሪክ ጨርሶ እንዲጠፋ በማድረግ የእነሱን ኑሮ ማደላደል አንዱ መገለጫቸው ነው፡፡
እኔ የምናገረው ከስሜተኝነት የተነሳ እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ግን የተረዳሁትን ያህል እናገራለሁ፡፡ ባለማወቅ ግን ልሳሳት እችላለሁ እኔ የተረዳሁት ስህተት ሊሆን ስለሚችል፡፡ የሚያርመኝ ካለም እቀበላለሁ፡፡ ደግሜ እናገራለሁ ከሥሜት የተነሳ አላወራሁም፡፡
በእኔ ግንዛቤና መረዳት በአለፉት አምስተ መቶና ምንአልባትም ከዚያም በላይ እንደ ኢትዮጵያዊው መሪ ሚንሊክ ያለ መሪ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካም ብቻ ሳይየሆን በአለም ላይ ነበረ የሚለኝን የታሪክ ምሁር ትንተና እሻለሁ፡፡ እኔ በአለፉት አምስት መቶ ከዚያም በላይ በሚሆን ዘመን እንደ ኢትዮጵያዊው ሚንሊክ ያለ ታላቅ መሪ እንዳልነበረ አስባለሁ፡፡ በእኛው ዘነድ ስለሚንሊክ ያለን ግንዛቤ ወይም ከላይ በጠቀስኳቸው የወረዱ አእምሮዎች የጎደፈ ወይም በእጅ የያዙት ወርቅ አይነት ብዙም ትኩረት ያልሰጠነው ይመስለኛል፡፡
ዛሬ በአብዛኞቻችን ዘንድ የሚንሊክ ታሪክ እንኳንስ የማንነታችን መገለጫ አድርገን የምንኮራበት በአንደበታችንም ለመናገር የሚቀፈን ሆኗል፡፡ ብዙዎቻችንም በመርዝ በተለወሰ ሌላ ታሪክ አእምሮአችን የታላቁን ሰው ታሪክ የሚያጎድፍ፡፡ በተለይም  በኢትርዮጵያ ትልቅ ቁጥር አለው ተብሎ በሚታመንለት ኦሮሞ እየተባለ በሚጠራው አብዛኛው ሕዝብ ዘንድ ዛሬ የሚንሊክ ጉዳይ ሲነሳ ያስበረግገዋል፤ እጅግ ያስቆጣዋል፤ ሥሙን አታንሱብኝ ይህን ሥም ከታሪክ ደምስሱት ጩኸት ያሰማል፡፡ ምክነያት ተብሎ ሲጠየቅ በዋነኝነት ብዙ ጊዜ የሚነሱት በሐረር የጨለንቆ ጦርነትና በአርሲ በሚንሊክ ዘመቻ ተፈጸሟል ተብሎ በዘበናውያን ታሪክ አዋቂዎች ነን ባሉ የተሰበከው የጡትና እጅ መቁረጥ (ሀርካ ሙራ ሐርማ ሙራ) ግፍ ነው፡፡
ሚንሊክን ታላቅ ከሚያሰኛቸው ታሪክ አንዱ ዛሬ ኢትዮጵያ ብለን የምንጠራትን አገር አንድ በማድረጋቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያን አንድ ያደረጉበት ሂደት ደግሞ አልጋ በአልጋ የነበረ ሳይሆን ከብዙ በየስፍራው በነበሩ መሳፍንቶች ጋር ተዋግተው ነው፡፡ በወቅቱ እንደአሁን ዘመን ዲፕሎማሳዊ ሂደት ብዙም የሚያስኬድ አልነበረም፡፡ ሆኖም ሚንሊክ እርግጥም ከዘመኑ በፊት የተፈጠሩ ታላቅ ሰው ስለነበሩ ዲፕሎማሳዊው ሂደት ሁል ጊዜም ቅድሚያ የሰጡት ነበር፡፡ አንድም መስፍን (የአካባቢ መሪ) የሚንሊክን ታላቅ ራዕይ ሳይቃወም ጦርነት የከፈቱበት የለም፡፡ በወቅቱ ግን በነበረው የመሳፍንቶች ኋላ ቀር አስተሳሰብ ከሚንሊክ የቀደመ አስተሳሰብ ጋር የሚጣጣም ባለመሆኑ የሚንሊክን አገርን የመገንባት ሂደት የሚተባበር አልነበረም፡፡ የእነዚያ ኋላ ቀር የአካባቢ መሪ ተብዬዎች ሕልም ለራሳቸው ከርስ የሚሞላ ሕዝብን ከመግዛት ያለፈ የዕድገትና ብልፅግና ሕልም ከቶውንም አልነበራቸውም፡፡ ይህ ደግሞ የሕዝብና የአገር ውርደትና ኋላ ቀርነት እንደ እሳት ለአንገበገበው ሚንሊክ እንቅፋት ነበር፡፡ በመሆኑም ሚንሊክ የወደደውን በውድ ያልወደደውን በግድ ማሳመን ይጠበቅባቸው ነበር፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ከብዙ ኋላ ቀር አስተሳሰብ ካላቸው የአካባባ መሳፍንት ጋር ጦርነት ገጥመዋል፡፡ በጦርነቶቹ ሁሉ የባለራዕዩ የበላይነት የግድ ቢሆንም ጦርነት ጦርነት ነውና ብዙ ጥፋቶች ጠፍተዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ግን የሰዎች ልጆች አልቀዋል፣ ተሰቃይተዋል፡፡ ይህ ሁሉ ግን የሚንሊክ ፍላጎት ሳይሆን የመሳፍነቶቹ ምርጫ ነበር፡፡
በሀረር ጨለንቆና አርሲ የተከሰቱ ጦርነቶች ሚንሊክ አገርን ለመገንባት ካደረጓቸው ሁለቱ ናቸው፡፡ የጨለንቆው ጦርነት በአስከፊነቱ ብዙ ሕዝብ ያለቀበት ቢሆንም በጦርነት ከሚከሰቱ የተለመዱ ጥፋቶች ሌላ ለየት ያለ የታሪክ ጠባሳ ያቆየ አልመሰለኝም፡፡ የአርሲው ጦርነት ግን እስከዛሬም ድረስ እንዲረሳ አጋጣሚን ለመጠቀም በሚፈልጉ መርዘኞች እንደ መሣሪያነት እያገለገለ ነው፡፡
ሀርካ ሙራ ሐርማ ሙራ! በአማርኛ እጅ መቁረጥ ጡት መቁረጥ ማለት ነው፡፡ ይህ አሳቃቂ ግፍ በአርሲው የሚንሊክ ዘመቻ ተከስቷል እየተባለ ዛሬ ባለው ትውልድ ልዩ ስፍራ የተሰጠው አልፎም ሐውልት የቆመለት ጉዳይ ሆኗል፡፡ እኔ እንዲህ ያሉ ግፎች በዚያ ዘመን በነበሩ ጦርነቶች ሊከሰቱ ከሚችሉ አሳቃቂ ክስተቶች አንዱ ሊሆኑ እንደሚችሉ አምናለሁ፡፡ ሆኖም በአርሲ ተከሰተ የተባለው እንዲህ ያለ ግፍ የታላቁ ሰው ሚንሊክ ትዕዛዝና ይሁንታ አለበት ብዬ አላምንም፡፡ በብዙ ጦርነቶች እንደሚከሰተው፣ ይልቁንም በዚያ የጠበቀ የጦርነት የመምራት አቅምና ቅንጅት በሌለበት ዘመን ከተዋጊዎች አንዱ ወይም ከዚያም በላይ እንዲህ ያለውን ጥፋት ፈፅመውት ይሆናል፡፡ ሚንሊክ ግን እንዲህ ያደረጉትን ወታደሮች ማንነት ቢያውቁ የሚሸልሟቸው እንዳልሆኑ አምናለሁ፡፡ ይልቁንም በሞት ሳይቀር ሊቀጧቸው እንደሚችሉ አምናለሁ፡፡ ይህ የሚንሊክ እውነተኛው ልብ ነው! ሚንሊክ እውነተኛ ጀግና የሚባል ባሕሪ ያላቸው ናቸው፡፡ ጀግና ደግሞ ጨካኝ አይደለም! ጀግና ጠላቶቹ የማይቋቋሙት እንጂ! እነኳንስ በሴቶችና አቅም በሌላቸው ላይ ሊያጠፋቸው የመጣን ጠላት እንኳን ከመግደል ይልቅ ከእነነፍሱ ይዘው ምህረትን ሊያደርጉለት የሚፈልጉ ናቸው፡፡ ጠላታቸውን እንኳን ገድለው በሬሳው ላይ የሚጨፍሩ አይደሉም፡፡ ይልቁንም አስቸጋሪና የተቋቋማቸው ጠላታቸውን ሲጥሉት ለአስከሬኑ ሳይቀር ክብርን የሚሰጡ ናቸው፡፡ እንዲህ ያለው ተቃራኒ ጠላት የሆነ ግን ጀግና አስከሬን ለውሻና ለአውሬ የሚሰጡ ሳይሆን በክብር የሚቀብሩ ውጊያውን የአላማ እንጂ የተፈጥሮ ጠላትነት እንዳልሆነ የሚያስቡ ናቸው፡፡ ሰውን በሰበዐዊነቱ የሚያከብሩ ልዩ አመለካከት ያላቸው ናቸው፡፡ ይህ የእውነተኞቹ ጀግኖች ልዩ መገለጫ ነው፡፡ ሚንሊክ ይህ ባሕሪ ልዩ መገለጫቸው ከሆኑ አንዱ ነበሩ! በነዚህ መስፈርቶች መሠረት ግን ብዙዎች በኢትዮጵያ ጀግኖች እየተባሉ የተወደሱትን ማንነት ቴዎድሮስን ጨምሮ እጠራጠራለሁ፡፡ ይልቁንስ በቅርብ ታሪክ የምናውቀው ሕወሐት አባል የነበረው ኃያሎም አረአያ እነዚህ የጀግኖች ልዩ መገለጫ ያልኳቸው ባህሪያት እንደነበሩት ብዙ የሰማቸው ገድሎቹ ይናገራሉ፡፡
እንግዲህ በስሜትና በጥላቻ በመረቀዙ አእምሮዎች ሳይሆን እውነትን ለመጋፈጥ በሚደፍሩ አእምሮዎች እኔ የተረዳሁትን የሚንሊክን ማንነት አይደለም የሚል ካለ ለማደመጥ እወዳለሁ፡፡ ሚንሊክ ሩሩህና ይቅር ባይነታቸው ባደረቸው ጦርነቶች ሁሉ በደረሱ እልቂቶችና ጥፋቶች እጅግ ይጸጸቱ ነበር፡፡ ችግሩ አማራጭ ብቻ በማጣታቸው ጦርነቱ ግድ ሆኖማቸው እንጂ፡፡ በደረሰው ጥፋት ካዘኑባቸው ጦርነቶች አንዱ ደግሞ የአርሲው ጦርነት ነው፡፡ በጦርነቱ አሸንፈው አገሩን ከተቆጣጠሩት በኋላም ወታደሮቻቸውን ሕዝቡ ባለማወቁ ምክነያት የደረሰበትን እልቂት አሳዝኗቸው ወታደሮቻቸውን አሸንፌያለሁ በሚል በሕዝቡ ላይ ሌላ በደል እነዳያደርጉበት አዋጅ አውጥተው ሁሉ ነበር፡፡ ለወታደሮቻቸውም የአርሲን ሕዝብ ሲገልጹት ወንድምህ የአርሲ ሕዝብ እያሉ ነበር እንጂ እንደ ጠላት አልነበረም፡፡ ይህን እውነታ የታሪክ አዋቂ ነን የሚሉት ለምን ለሕዝብ ለማሳወቅ አልፈለጉም፡፡ ይልቁንስ የሚንልክ ትዛዛዊ ግፍ ለመሆኑ አጠራጣሪ ስለሆነው ሀርካሙራና ሀርማ ሙራ ማግዘፍን ለምን ፈለጉ፡፡ ሌላው የሚንሊክ ማንነት የተገለጸበት ጦርነት የወላይታው ከንጉስ ጦና ጋር የነበራቸው ጦርነት ነው፡፡ ንጉስ ጦናን አሸንፈው በእጃቸው ካገቡና አላማቸውን ከአሳመኗቸው በኋላ ንግሰናቸውን አጽድቀው እንደሾሟቸው ይነገራል፡፡ ከዚያም በላይ ጦና በጦርነቱ በመቁሰላቸው ምክነያት ሌላውን ሰው ባለማመን ሚንሊክ ራሳቸው እየተከታተሉ እንዲታከሙ ማድረጋቸው ይነገራል፡፡ ሌሎችም አያሌ የሚንሊክን ሕይወት የሚናገሩ መዛግብቶች ሩሩሕና የጅግና ሰው ልዩ መገለጫ የሆኑትን ባሕሪያቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ሚንሊክ ጋር በቀል የለም ጭጋኔም የለም የአላማ ጽኑነትና ታላቅነት እንጂ፡፡ ዘረኝነትም የለም ሰበዐዊነት እንጂ፡፡ በሚንሊክ አስተዳደር ወቅት ኢትዮጵያ ዘመናዊ በሚመስል ፌደራሊዝም ትተዳደር እንደነበር ስነቶቻችን እናውቃለን? አንዳንድ የሚንሊክን አላማ ለመረዳት እመቢ ባሉ መሳፍንት በቀር ከጦርነት በኋላ ሳይቀር ለእነዚያው የተዋጓቸው መሳፍንት ስልጣንን በሰጠት የራሳቸውን አካባቢ እንዲያስተዳድሩ ያደርጉ ነበር፡፡ በወቅቱ የተሸለ ግንዛቤ የነበራቸው እንደነ አባ ጅፋር የጅማው ያሉ የሚንሊክን አላማና ራዕይ ለመረዳት ስላልተቸገሩ በሠላም በአገር አንድ ማድረጉ ሂደት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የሚንሊክ እውነተኛው ታሪክ ዛሬ ኢትዮጵያ ብለን የምንጠራትን አገር የፈጠሩ፣ አለም ላይ በእሳቸው ዘመን ኡሉ የተባሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ወደ አገር ያስገቡ እነዚህም ስልክ፣ ኤሌክትሪክ፣ መኪና፣ ባቡር፣ ሌሎችም፣ አገርን በዘበናዊ አስተዳደር እንድትመራ የዋቀሩ (ሚኒስቴር መሠረት ያደረገ) ሌሎች ብዙ በአንድ ሰው እድሜ ሊሰሩ የሚችሉ የማይመሰሉ ብዙ ራዕዮችን በተግባር ያስጀመሩ ናቸው፡፡ ይህን ሁሉ ማድረጋቸው ሳያንስ ሚንሊክን ከቅርብ ወዳጅ እስከ ሩቅ ባላአንጣዎቻቸው እጅግ ፈታኝ መነቆዎች ነበሩባቸው፡፡ በወቅቱ ባለው ኋላቀር አመለካከት ምክነያት ብዙ የቅርብ የተባሉ የቤተመንግስቱና የቤተክህነቱ ሰዎች እንቀፋቶች እንጂ ለሚንሊክ አጋዥ አልነበሩም፡፡ በሚንሊክ የአገር አንድ የማድረግም ሆነ አገርን ወደ ዘመናዊነት መቀየር ሂደት በተሻለ ወሳኝ ሚና የነበራቸው የውጭ አገር ሰዎችና አንዳንድ የቅርብ አባሮቻቸው ናቸው፡፡ ከቅር አባሮቻቸው ደግሞ በተለይም አገርን አንድ በማድረጉ ሂደት የሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝቦች ከየትኛውም የኢትዮጵ የሕብረተሰብ ክፍል ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡ የሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪ በታሪካዊው የአድዋው የሚንሊክ ድልም እንደዛው ከሌሎች በተለየ ነበር፡፡
ዛሬ ላለው አብዛኛው የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ ግን የሚንሊክም ታሪክ እነዛ የሚንሊክ የቀኝ ክንድ የነበሩት ኦሮምኛ ተናጋሪ ሸዌዎችም የሚታየው በበጎ ሳይሆን በጥላቻ ነው፡፡ ምክነያቱ ደግሞ የታላቅ ባለራዕዮች ሕልም የማይገባቸው፣ በተንኮል የነወረ አእምሮ ይዘው ታሪክን በማጉደፍ ትውልድን በእነሱ በተመረዘ አእምሮ ለመበከል ያሰራጩት መርዝ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ለአሁኑ ትውልድ የበለጠ የታሪክ ትውስታና ክፉውም ደጉም ከሞላ ጎደል ከሚታወቀው የደርግና የኃ/ሥላሴ ዘመን ስህተቶች ይልቅ የሚንሊክ ዘመን ስህተትን አቅርቦና አግዝፎ ለማሳየት የተመረዙ አእምሮዎች የሚፈጥሯቸው ሀተታዎች ብዙ ናቸው፡፡ ምክነያቱ ግልጽ ነው አሁን ያለው ትውልድ የሚንሊክን ዘመን እውነተኛ ነገሮች በአካል የሚመሰክርለት የለውም ስለዚህ ምስክር በሌለበት በመሰሪዎቹ አእምሮው ሊመረዝ የሚችለው በቆየው ታሪክ እንጅ በአካል ያሉ መስካሪዎች ባሉበት ታሪክን ለመዋሸት ስለማይመች ነው፡፡ ሌላው ሚንሊክ የሠሩትን ታላላቅ ሥራዎች በበጎነቱ ማንሳቱ ራስን የሚያሶቅስ አደጋ ስላለው ነው፡፡ ዛሬ ላለው ትውልድ የሚንሊክ ዘመን ራዕይ ባለዕዳ አደርጎታልና ነው፡፡ በሚንሊክ ዘመን ራዕይ ይህች አገር ቀጥላ ቢሆን የት በደረሰች ነበር፡፡ ሌላው የሚንሊክ ራዕይ የአገር አንድነትና ብልፅግና ልዩ መሠረት ሥለነበር ይህንን መሠረት ሳያፈርሱ ስለዘረኝነት፣ ቀበሌ ዝቅ ብሎም ስለ ጎጥ እንዲያስብ ሕዝብን ማምከን አይቻልም፡፡
ዛሬ ከየትኛውም ክልል ትልልቅ ከሚባሉ ክልሎች በሚያሳዝን ሁኔታ የኦሮምያ ክልል በልማቱም ሆነ በመልካም አስተዳደሩ ወደ ኋላ መቅረቱ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፡፡ መሠረታዊ ምክነያቱ ሕዝቡን ከሌሎች ጋርም ሆነ እርስ በእርስ ትብብር እንዳይኖረው የጥላቻን ዘፈን እየዘፈኑለት የራሳቸውን ኑሮ በተፈጠረላቸው አጋጣሚ እንደ ልባቸው የሚኖሩ ኦሮሞ ነን ባይዮች አደገኛ ዜጎች ናቸው፡፡ ይህንን ከሚያክል ትልቅ ክልልና ሕዝብ አይደለም ኢትዮጵያን ሊመራ የሚችል ክልሉን ሊመራ የሚችል ሰው ታጥቷል፡፡ ኦሮሞ ነኝ የሚለው አብዛኛው የዛሬው ትውልድ ትልቁ እርካታው የሌሎች መውደቅ በተለይም ነፍጠኛ እያሉ የሚጠሩት የአማራውና አሁን በስልጣን ላይ በብዛት እንደተወከለ የሚነገርለት የትግራይ ሕዝብ ውድቀት እንጂ የራሱ ብልጽግና አይደለም፡፡ ለኦምኛ ተናጋሪው ክልል በልማትና በአስተዳደር ወደ ኋላ መቅረት ቁጭት ተሰምቶት ሊሰራ ከሚሞክር መሪና ትውልድ ይልቅ ከብዙ አመታት በፊት የተፈጠሩ የታሪክ ስሕተቶች ደግሞደጋግሞ በማላዘን ሌላ መርዛማና በጥላቻ የተበከለ ትውልድ ለማዘጋጀት ተግቶ የሚሰራው በዝቷል፡፡
ዛሬ ኦሮምኛ ተናጋሪ ሆኖ ያለው ሕዝብ በዘር (በደም) አንድ እንዳልሆነ ግልጽ ነው፡፡ በደም ግንድ ከሆነ የወለጋና ሐረር ኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ ከሚቀራረበው በላይ የጎጃ አማርኛ ተናጋሪውና የወለጋ ኦሮምኛ ተናጋሪው ይቀራረባሉ፡፡ የባሌና ሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች ከሚቀራረቡት በላይ የሸዋ ኦሮምኛ ተናጋሪና የሸዋ አማርኛ ተናጋሪ የበለጠ የደም ትስስር አላቸው፡፡  በባህልም ቢሆን እንደዚያው ነው፡፡ ዛሬ ዘረኝነትንና የቀበሌ አስተሳሰብን የሚሰብኩ ግን ቋንቋን ተመርኩዘው ግዙፉን ሕዝብ በአንድ ከአጨቁትና ከሌሎች ጋር ሕብረት እንዳይኖረው ከአወሩት በኋላ ወደታች ደግሞ በጎሳና፣ ቀበሌ፣ ዝቅ ብለው በጎጥ ይሸነሽኑታል፡፡ የኦሮምኛ ተናጋሪው ሕዝብ ከሌሎች በአካባቢው የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች ያልተጋጨው የለም፡፡ ምክንያቱ ግልጽ ነበር፡፡ ሕዝቡ ለሌሎች ጥላቻ እንዲኖረው ስለሚሰበክ ነው፡፡ አልፎም ይሄው መለያየትን የሚሰብከው መዝሙር እርስ በእርስ ሳይቀር ጥላቻንና ግጭትን አስነስቶ አይተናል፡  እንደወንድማማች የሚተያዩት ጉጂና ቦረናን ሳይቀር ለከፍተኛ ደም መፋሰስ ዳርጓል፡፡
ይሄው ሃያ ምናምን አመት ሙሉ ስለቀድሙት ገዥዎች ጭቆናና በደል ሲነግሩን፡፡ የቀደሙትስ ጨቋኝና ጨካኝ ሆነው የኦሮሞን ሕዝብ ሲበድሉት ኖሩ ተብሎ ይታሰብ ዛሬስ የዚያን ዘመን በደል ሊያስረሳ የሚችል መሪ እንዴት ከዚህ ትልቅ ሕዝብ መካከል ጠፋ፡፡ እውነታው የቀደሙት ጨካኝና በደል አድርሰውም ከሆን ለኦሮምኛ ተናጋሪው የተለየ አልነበረም፡፡ ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ አማርኛ ተናጋሪ ከነበረው ይልቁንም የነገስታቱ ወገን ነው ተብሎ ከሚታመነው የሸዋ አማርኛ ተናጋሪ ሕዝብ በቀድሞ ነገስታት የተሻለ ተጠቃሚ እንደነበር እናውቃለን፡፡ ሌላው ቀርቶ የነገስታቱ የቅርብ አጋር እየተባለ ዛሬም ድረስ በሌላው የኦሮምኛ ተናጋሪ በጥሩ አይን የማይታየው የሸዋው ኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ በነገስታቱ ዘመን አንዳች ተጠቃሚ እንዳልነበረ አእምሮ ካለን እናስተውላለን፡፡ ለእነዚህ ሕዝቦች ከሌላው በተሻለ የቀረላቸው ሀብት ቢኖር ሌላውን በጥላቻ አለመመልከት ለአገር አንድነትም ልዩ ፍቅር መኖር ነው፡፡
ሌሎች ክልሎች በአቅማቸው ልማታቸውንና የአስተዳደርም ችግራቸውን በፍታት ልዩ መንገድን እየሄዱ ይገኛሉ፡፡ በተለይም የቀድሞው ገዥና ጨቋኝ ተብለው የተፈረደባቸው የአማርኛው ተናጋሪ ሕዝብ ክልል  በቁጭት በሚመስል ሁኔታ እያደገ ለመሆኑ ግልጽ እየሆነና ልዩነቱንም ከሌሎች እያሰፋ መሆኑን እያሳየን ይገኛል፡፡ ትግራይ የገዥውን መንግስት ድጋፍ እያገኝ ስለሆነ ነው እየተባለ ቢታማም እውነታው የእድገት ጥማት ባላቸው መሪዎች ምክነያት እንጂ የማዕከላዊው መንግስት ተፅዕኖ ብቻ እንዳልሆነ እናያየለን፡፡ ደቡብና ሌሎች አናሳ እይተባሉ የሚጠሩ ክልሎች ሳይቀር ከኦሮምያ በተሻለ ዕድገት እያሳዩ ናቸው፡፡ በማዕከላዊውም መንግስት ያላቸው ተሳትፎ ከኦሮምያ ይልቅ የደቡብ የተሻለ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ ምክነያቱ ግልጽ ነው ኦሮምያ ኢትዮጵያን በሚወክል አመለካከት ይቅርና ክልሉን እንኳን በሚወክል አመለካከት የተገነባ ሰው ታጥቶበታል፡፡ በደቡብ ብዙ ሕዝቦች ኢትዮጵያዊ መሠረትን በደንብ ያደበሩ ናቸው፡፡ በኦሮምያ  ሌሎችን በመጥላት የተጀመረው ሂደት ዛሬ ወርዶ ቀበሌ ደርሷል፡፡ ወለጋው ወለጋውን፣ አርሲው አርሲውን፣ ታች ወርዶ ደግሞ ሻንቡ ሀረቶ ምናምን እያለ የሚከፋፍል ነው፡፡ ይህ አይነቱ ባሕሪ በሌሎች ክልሎች አይንጸባረቅም ሳይሆን በንጸባረቅም ሌሎች ሌሎችን ጨምረው በሚያማክሉ ከፍተኛ ባለአእምሮዎች ይመክንና ቀበሌ ከሆነ ቀበሌ፣ ከፍ ብሎ በክልልም ከሆን ክልሉን ሳያልፍ ይመክናል፡፡ ኦሮምያ ግን እንደዚያ አይደለም፡፡ የወረደውን የጎጠኝነት ስሜትና አመለካከት የሚያመክን ጠፍቶ ትውልዱ በአብዛኛው በወረደው ጎጠኝነት ስሜት መክኗል፡፡
አሳዛኙ ነገር ተማርን የተሸለ የሕወት ልምድ አልን በሚሉት ይህ የአመለካከት ወርደት በርትቷል፡፡ በተለይም ደግሞ በተለያዩ መንገድ ወደ ውጭ ሄዶ በሚኖረው የኦሮምኛ ተናጋሪው ለሌሎች ያለው ጥላቻ እጅግ የከፋ ነው፡፡ አማራ ወይም ትግሬ የሚባለውን በመጥላት ሌሎችን ይጋብዛል፡፡ ሌሎችንም ወንድም እንደሆነ ሊሰብክ ይሞክራል፡፡ ይህ ጥላቻን ያዘለው ስብከት ከትልቋ ኢትዮጵያ እስከ ታች ተራ ግለሰቦች ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡ በቅርቡ በቴዲ አፍሮ ምክነያት የበደሌን ቢራ ላለመጠጣት የተደረገው አድማ አንዱ ሕዝቡ እንዴትና በምን አይነት አመለካከቶች እንደሚመራ በሌላውም ላይ ያለው ጥላቻ ምን ያህል እንደሆነ ያመላከተ ነበር፡፡  ይህን ለሚያሕል አደማ ደግሞ ያደረሰው በሌሎች ከፍተኛ አደናቆትን ያተረፈው የቴዲ አፍሮ  ጥቁር ሰው የሚለው ዘፈኑ እንደነበር ግልፅ ነው፡፡ የቴዲው ጥቁር ሰው ሚንሊክ ግን ለአፍሪካ ሳይቀር ኩራት እንጂ የሚያሳፍር አልነበረም፡፡ በጥላቻ የተመረዘው የእኛው ኦሮምኛ ተናጋሪ ግን ያንን የጥቁር ሕዝብ ሁሉ ክብር የሆነውን ታሪክ ለመስማት አለመፈለግ ብቻም ሳይሆን ያንን ታሪክ የሚያነሱትን በሚያገኘው አጋጣሚ ሊበቀል እንዳለው አየን፡፡ አሁን ያለው እንዲህ የተመረዘው የኦሮምኛ ተናጋሪ ትውልድ ግን ስለሚንሊክም ሆነ በዘመኑ ስለነበሩ ክስተቶች በውል የሚያውቀው ነገር የለም መርዛማና የራሳቸውን ልዩ ፍላጎት በሕዝቡ ሊያሳኩ የሚያሴሩትን ስብከት ተቀበለ እንጂ፡፡
በቅርቡ የሀረካ ሙራ ሐርማ ሙራ መታሰቢያ በሚል አንድ ሐውልት ተመርቋል፡፡ እኔ እውነትም ይህ ክስተት በየትኛውም ስህተት ቢሆን ተከስቶ ከነበረ መታሰቢያ መቆሙ ክፋት አለው ብዬ አላምንም፡፡ ሆኖም ክስተቱ ተፈጠረ ከተባለ ከስንት ዘመን በኋላ ዛሬ ሀውልት ለማቆም የታሰበበት አላማ ያንን ክስተት ለማስታወስ የተደረገ ሳይሆን ይልቁንም ጥላቻን ለማጠናከር እንዲህ ያደረገሕ ሕዝብ ነበር ለማለት የቆመ ሀውልት ሆኖ ነው የተሰማኝ፡፡ አሁን አሁን እንደውም ያ አሳቃዊ ክስትት ሆን ተብሎ የተፈጠረ ታሪክ ነውም ብዬ እየተጠራጠርኩ ነው ከሌሎች ጋር ጥላቻ እንዲፈጠር የሚደረገው ሴራ ብዙ ነውና፡፡  ይህ ሀውልት በተመረቀበት በዚህ ሰሞን የሩዋንዳውም እልቂት ሃያኛ ዓመት የሚታሰበበት ነበር፡፡ ሲታሰብ ግን ልዩ መልዕክት የነበረው የተፈጠረውን ክስተት የሚያስረሳ ሰላምንና የአገር ብልጽግናን በዚያች አገር የማምጣት ራዕን ነው፡፡ ሐውልት እነኳን ለእነዚያ ዜጎች መታሰቢያ ማቆም ቢያስፈልግ ዳግም እንደዚያ ያለ አረመኔነት በዚያች አገር እንዳይከሰት ለትውልድ ማስተማሪያነት እንጂ ቂም በቀለኝነትን ለማቆየት አይሆንም፡፡ የኦሮምያው የሀርካ ሙራ ሐርማ ሙራ ሐውልት ግን ግልጽ መልዕክቱ ሌሎችን በመጥላት የተመረዘውን ብዙ የኦሮምኛ ሕዝብ የበለጠ ጥላቻ እንዲያድርበት ሌሎችም ሌሎችን በመጥላት ተሳትፎ እንዲያደርጉ የታለመ ነው ብዬ አመንኩ፡፡  
ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ በኢትዮጵያ ታሪክም ሆነ የወደፊት ብሩሕ ራዕይ ደስተኛ አይደለም፡፡ እነዚህ የሕዝቡ አካላት የኢትዮጵያን ውድቀት እጅግ የሚመኙ ናቸው፡፡ ሌላ ቀርቶ ከኢትዮጵያ ጋር የተያያዘ ወይም እነሱ በጣም ከሚጠሉት አማራ ወይም ትግሬ ከሚባለው ሕዝብ ጋር የተያያዘ የራሳቸው ነገር እንኳን እርም ነው፡፡ የአባይ ወንዝን እንደምሳሌ ላንሳው፡፡ የአባይ ወንዝ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ ብዙ ይነሳል፡፡ መነሻው ደግሞ ጎጃም የጮቄ ተራራ ነው፡፡ ሆኖም አባይን በውል የምታውቁት ካላችሁ አባይን አባይ ያደረገው የጮቄ ተራራ ወይም ከጣና የቀዘፈው ውሀ ሳይሆን ከኦሮምያ የሚነሱ ታላላቅ ወንዞች ናቸው፡፡ በተለይም ደዴሳና ዳቡስ፡፡ ይሄንን ለማስተዋል አሁን ግድብ እየተሰራበት ያለውን ቦታ የሚፈሰውን ውሃና ወደጎጃም ስትሻገሩ የምታዩትን ውሃ አስተውሉ፡፡ ግብጾቹም ይሁኑ ሌሎች እንቅልፍ የሚነሳቸው ጎጃም ያያችሁት አባይ አይደለም ደቡስና ዴዴሳ የደለቡት አባይ እንጂ፡፡ የአባይ ሥም ሲነሳ ግን ብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ ጥሩ ስሜት የለውም፡፡ ግድቡን ጨምሮ ሌሎች ለኢትዮጵያ ብልጽግናም ትልቅ ድርሻ ያላቸው ልማቶችም እንዲሁ በብዙ የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕዝብ በመልክም አይታዩም፡፡ ግን ለምን? የሚንሊክን ታሪክና ዘመን እንዲህ በጥላቻ የሚያስመለክትስ በእውን የተጨበጠ ይቅር የማያሰኝ ስህተት አለ? ካለስ ይህ ትውልድ እነዴትና በምን ምክነያት እነዚያ ስህተቶች እንደተከሰቱ ምን ያህል ተረድቶ ነው እንዲህ በጥላቻ የተመረዘው?! ነው ወይስ አሁንም እያየን እንዳለንው የኢትዮጵያ ነገር ስለማያደስተው ከኢትዮጵያዊነት ጋር የተቆራኘውን የአገሪቱን መስራች ሚንሊክን በስሜት ብቻ መጥላት ይሆን?
ኦሮምያ ውስጥ ባለፉት ሃያ ምናምን አመት ከተከሰተው ግፍ በላይ በቀደሙ የታሪክ ጊዜያት ለመከሰቱ ጥያቄ እያጫረብኝ ያለ ጉዳይ ነው፡፡ ብዙ ጥያቄዎች አሉ! ኦሮምያ የሚባለውም ክልል ይሁን ኦሮምኛ ተናጋሪ የተባለው ሕዝብ ግልጽ በሚታይ ሁኔታ እየተቀደመ እንደሆነ ይረዳ፡፡ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ይህ ልዩነት ጎልቶ ሲታይ ይህችን መልዕክቴን ያነበቡ ያስታውሱ ይሆናል፡፡  ግን ለምን???!!
የታላቋ ቀን ልጅ ሚያዝያ 1 2006 ዓ.ም.