Thursday, September 18, 2014

“ክልክል ነው”

“ክልክል ነው”

(በእውቀቱ ስዩም)
not allowed
ማጨስ ክልክል ነው
ማፍዋጨት ክልክል ነው
መሽናት ክልክል ነው
ግድግዳው በሙሉ ተሰርቶ በክልክል
የቱ ነው ትክክል?
ትንሽ ግድግዳና ትንሽ ኃይል ባደለኝ
“መከልከል ክልክል ነው”፤ የሚል ትዕዛዝ አለኝ፡፡
(በእውቀቱ ስዩም፣ የ፣ሣት ዳር ሐሳቦች፣ 2000)

በጎደሬ ወረዳ የዘር ግጭት ተነሳ፤ መከላከያ ገብቷል

በጎደሬ ወረዳ የዘር ግጭት ተነሳ፤ መከላከያ ገብቷል

የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች ከነቤተሰቦቻቸው ተገደሉ
gode-rie
በጋምቤላ ዞን በጎደሬ ወረዳ ነጋዴዎችና ሰፋሪዎች ከአካባቢው ተወላጅ የመዠንገር ጎሳ አባላት ጋር ተጋጩ። በግጭቱ ከ17 ሰባት በላይ ሰዎች ተገድለዋል። በግጭቱ የመዠንገር ዞን አስተዳዳሪና የጎደሬ ወረዳ ዳኛ ከነቤተሰቦቻቸው የግጭቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። ግጭቱን ለማብረድ የመከላከያ ሠራዊት የገባ ሲሆን፣ የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ በጉዞ ላይ እንዳለ በተሰጠ መመሪያ እንዲመለስ ተደርጓል
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለጎልጉል እንደገለጹት በወረዳው በመሬት ባለቤትነትና በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ከመሀል አገር በመጡ ሰፋሪዎችና ነጋዴዎች መካከል አለመግባባት ከተፈጠረ ዓመታትን አስቆጥሯል። የፌዴራል አገዛዙም ሆነ የክልሉ አመራሮች ችግሩ ሳይሰፋ ሰላማዊ መፍትሄ ባለማፈላለጋቸው ችግሩ ሊካረር ችሏል። ኢህአዴግ የሚከተለው በዘር ከፋፍሎ የመግዛት ፖሊሲ ለችግሩ መባባስ በዋንኛነት ተጠቃሽ ነው።
ባለፈው ሃሙስ በአንድ የመሃል አገር ሰፋሪና የአካባቢው ተወላጅ በሆነ አርሶ አደር መካከል ድንገተኛ ጸብ ተነስቶ ነበር። በጸቡ የመዠንግር ጎሳ አባል የሆነው አርሶ አደር ህይወት አለፈ። በጎሳ አባላቸው መገደል የተበሳጩ ዘመዶች ውሎ ሳያድር በወሰዱት የበቀል ርምጃ አንድ ሰፋሪ የመሃል አገር ሰው ህይወት አለፈ። እንደ ዜናው አቀባዮች ከሆነ በዚሁ በመሬት ጉዳይ በተከሰተው የሁለት ግለሰቦች ህልፈት ተከትሎ ችግሩ ተካረረ።
በተመሳሳይ ቀን ማምሻው ላይ ከመሃል አገር የመጡት ሰፋሪዎች የዞኑን አስተዳዳሪ፣ ባለቤታቸውንና ሁለት ልጆቻቸውን መኖሪያ ቤታቸው በመሄድ በስለት ገደሉ። በተመሳሳይ አንድ የጎደሬ ወረዳ አስተዳዳሪ ከባለቤታቸውና ከልጃቸው ጋር ተገደሉ። በደቦ የተጀመረው የስለት ግድያ እየሰፋ የሟቾችን ቁጥር 17 እንዳደረሰውና በስለት የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከ40 በላይ መሆኑን በስልክ የገለጹት ያካባቢው ነዋሪዎች “አሁን ፍርሃቻ አለ። ቤት ለቤት የተካሄደው ግድያ የት ጋር ያቆማል? የመከላከያ ሠራዊት ሚናም ግልጽ አይደለም” ብለዋል።
goderieየጋምቤላ ዞን ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ እየገሰገሰ ባለበት ወቅት ከአዲስ አበባ በተሰጠ ትዕዛዝ ወደ ጋምቤላ እንዲመለሱ መደረጉን ያመለከቱት እኚሁ ክፍሎች፣ “የጋምቤላ ልዩ ኃይል ግጭቱ ያለበት ቦታ ሲደርስ በራሱ ክልል ሰዎች ላይ መጤዎች ጉዳት ማድረሳቸውን ሲመለከት ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ግጭት ሊፈጠር ይችላል” በሚል ስጋት የልዩ ኃይሉ ወደ ጋምቤላ የተመለሰበትን ምክንያት ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
በገጀራና በተለያዩ የስለት መሳሪያዎች የተካሄደው ግድያ የሚዘገንን እንደነበር፣ ቀን ጠብቆ ተጎጂው አካል ከመበቀል ወደኋላ እንደማይል፣ በስለታማ ቁሶች የሚከናወነው ግድያ ሊሰፋ እንደሚችል ስጋታቸውን አክለው የገለጹት ነዋሪዎች ኢህአዴግ ሰላማዊ መፍትሄ ሊፈልግ እንደሚገባ ከወዲሁ ጠይቀዋል። በጋምቤላ ክልል በሳንቲም የሚቸበቸበውና የተፈጥሮ ደን እያወደመ ያለው ኢንቨስትመንት የተወሳሰበ ችግር ማስከተሉ አይዘነጋም። በዚሁ ሳቢያ በርካታ ንጹሃን ህይወታቸው ማለፉ የሚታወስ ነው። ክልሉን ከላይ ሆነው የሚመሩት አቶ አዲሱ ለገሰ መሆናቸው ይታወቃል።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ጉዳዩን አስመልክቶ ከኦስሎ ለጎልጉል አስተያየት ሲሰጡ “ባሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ላለፈ ወገኖች የሰላም ረፍት ይሁን፣ ፍትህ በልጅ ልጆቻችሁ ትፈርድላችኋለች፣ ፍትህ ሩቅ አይሆንም” በማለት ነበር የጀመሩት። አያይዘውም “ምንም እንኳ ባል ፖለቲከኛ ቢሆን ሚስትና ልጆች ምን አደረጉ? ህጻናትና ሴቶች በማያውቁት ጉዳይ ለምን ሰላባ ይሆናሉ? ቀደም ሲል አብረው የሚኖሩ ሰዎች ዛሬ ለምን ይጋጫሉ?” ሲሉ ችግሩ ሁሉ የሚመነጨው ኢህአዴግ ከሚከተለው ጎሳን መሰረት ያደረገ የከፋፍለህ ግዛው መርህ አንደሆነ ገልጸዋል።
“መመሪያ ሰጪው፣ ገዳዩ፣ አስገዳዩ፣ ቆሞ ተመልካቹ፣ … ሁሉም ከፍትህ አደባባይ አያመልጡም” ያሉት አቶ ኦባንግ “ዘርን እየለየ የሚከናወን ግድያ “ጄኖሳይድ” ነው። አኙዋኮች ላይ በጅምላ ከተከናወነው ጭፍጨፋ ለይተን አናየውም” ሲሉ በጉዳዩ ክፉኛ ማዘናቸውን አመልክተዋል።
የሚመሩት ድርጅት ጉዳዩን በቅርብ እየተከታተለና አስፈላጊ ነው የሚለውን ስራ እያከናወነ እንደሆነ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ ሁሉም ያካባቢው ነዋሪዎች ሰፋሪም ሆነ የቀዬው ተወላጆች እንደቀድሞ በፍቅር ሊኖሩ የሚያስችላቸውን እሴቶች እንዲጠብቁ መክረዋል። በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች ጎሳን እየለየ የሚካሄደው ግድያና ማፈናቀል እየሰፋ እንጂ እየቀነሰ ባለመሆኑ ስጋቱ ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል። በዚህ ከቀጠለና ህወሃት የቀበራቸው የጎሳ ፈንጂዎች ሲነዱ እሳቱ ሁሉንም ስለማይምር ሁሉም ዜጎች ጥንቃቄ እንዲወስዱ አሳስበዋል። ኢህአዴግም ችግሮችን ከማስፋት ይልቅ የሚቃለሉበትን አግባብ ለራሱ ሲል ሊከተል እንደሚገባ ጠቁመዋል። ጎልጉል የዞኑንና የወረዳውን አስተዳደር ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ይሁን እንጂ የክልሉ ፖሊስ ዝርዝር መግለጫ ባይሰጥም የተባለው ቀውስ ስለመፈጠሩ አልካደም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Friday, September 12, 2014

ሰሞኑን ኢትዮጵያዊው መምህር ግርማ ወንድሙን ለማግኘት ከመላው አውሮፓ እና አሜሪካ ወደ ስዊትዘርላንድ የመጡት ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ቁጥር ከተጠበቀው ከ5 እስከ 6 እጥፍ ሆኖ በመገኘቱ ለፀጥታ ያሰጋል በማለት ፖሊስ ስነ ስርአቱን እንዲቋረጥ አድርጓል።

 Ethiopian healer causes chaos in Altstetten, Switzerland


A miracle healer from Ethiopia has attracted over 5000 visitors in Zurich complex 457 – where 300 to 700 were expected. For security reasons the police cleared the building.
If you were driving through the Hohlstrasse in Altstetten on Saturday afternoon, you probably stuck in a traffic jam. Thousands of people were running, according to a reader-reporter on the street. VBZ-employees had to regulate the traffic so that an even greater chaos wouldn’t materialize. “Hundreds of strollers were parked outside the complex 457″, says the reader reporter.
Responsible for the onslaught was the Ethiopian priest Memehir Girma Wondimu. “He can mentally and physically heal the sick,” says Mistre Haile Selassie, OK Member of the healer events in the complex. He had expected around 1,000 visitors. “But there were five or six times more.” People had traveled from all over Europe and even the United States. “Most of them came originally from Ethiopia and Eritrea.”
sw6 sw5 sw4 sw3 sw2
“Security was no longer guaranteed»
According to Marco Cortesi, media director of the Zurich city police, the organizers had announced 300 and 700 visitors: “Ultimately, however, it was around 2500 in the complex – and additional crowd of 2000 to 3000 were waiting outside.” Since security was no longer guaranteed, the police had to intervene at 2 clock. “The evacuation went smoothly – the priest was very cooperative,” says Cortesi.
Organizer Haile Selassie does understand the situation. But he is sad the priest couldn’t stay until Sunday as planned. “Many visitors traveled in vain.” But still, Wondimu has healed a paralytic in Zurich, among other things, says Haile Selassie.

ethiotube.....