Friday, January 31, 2014

ዬማረተ ማጭድ ሸክም፤ በሀቅ ጭብጥ ይረታል።


ከሥርጉተ ሥላሴ (ሲዊዘርላንድ ዙሪክ)
ንጋት ላይ እንደ ሀገሬ ገበሬ ካሊሜን ተከናንቤ ጉብ አልኩ። ያው ብራና እና ኮቢን በማገናኘት ሰንበት ላይ ከእናንተ ከውዴቼ ጋር ለመታደም ፈለግሁ። ከተሳካና ሃሳቤ ተሳክቶ ጡሑፌ መልክ ከኖራት መንገዱ ጨርቅ ያደርግላታል። ይገርማችኋል … በነፃነት አንደበት እርምቷን፣ ወቀሳዋን፣ ነቀሳውን ለመቀበል ተሰናድታለች። ሸብ አድርጋ መልካሙን መቀነት ተድባ ሽብሽቦዋ ላይ፤ ከራሷ ተረከዝ ላይ ደግሞ ቀልቤዋን ውሽክ አድርጋ፤ ለስታዋን ከአናቷ በፈገግታ አውጣ እንሆ ገሰገሰች ናፍቆቶቿን ፍለጋ …. የሀገሯ ጠረን ሽው አላትና … አሁንማ በተያዘ በተረዘዘው ጠብታ ጠሪ ሆነች …
እንዴት ናችሁ ውዶቼ? … ያላመረኝ ነገር ሲከነክነኝ ሰነበተ። የትውልዱ መንፈስ ጤናማ ሆኖ ብክል የሚያደርጉ ጠንጋራ አመለካከቶች በወጉና በጊዜው ካለተቀጡ፤ ነገ መርቅዘው ካለአቅማና ካለወርዳቸው ታሪክን በመጋፋት እንዳይንጠራሩ በማሰብ በተገቢው ተዳስስው መልክ መያዝ ያለባቸው ጉዳዮች በጥልቅ ዕይታዎች ካለፈው ግርምታ ጹሑፌ ጋር ታዳሚ ቢሆኑም፤ በተናጠል አውጥቶ ብልታቸውን እንደ አግባብነታቸው ማዬት ግን ግድ ሆነ። ሲበተን – ሲረጭ እዬቆ ሲሄድ መርዝ እንደ ማገናዛቢያ ተቆጥሮ እሳት እንዳይጭር ሚዛን ላላቸው የነገ ሀገር ተረካቢዎች ማነፃጸሪያ ሥራዎችን መሥራት ያስፈልጋል። obang
በቅድሚያ ግና አንድ የጸሁፌ ታዳሚ ለሰጡኝ ገንቢ አስተያዬት ቅድሚያ መስጠትን ወደድኩ። ባለፉት ጹሑፌ „ሞገደኛው ተክሌ“ እይልኩ ነበር የፃፍኩት። ታዳሚዬ እንዲገነዘቡልኝ የምሻው ይህን ስም እኔ ሳልሆን እራሱ የተጠቀመበት ስለመሆኑ መግለጽ እፈልጋለሁ „ጥምረት“ እንደ ተመሰረተ …..
ሞገደኛው ተክሌ በነሃሴ 29.2011 ላይ “ታየኝ እኮ፡ ሀረርና ወለጋ ገጥሞ፡ የ“ኦሮሚያ”ን ሪፐብሊክ ሲመሰርት ችግሩ ግን፡ ግንቦት ሰባትና እኛ ጋር ነው።“ https://ecadforum.com/Amharic/archives/621/ የዛሬን ያላዬ …. ወቼ ጉድ …
እራሱ የሰጠው ሥም ነው። ደግሞ „ሥምን መላእክ ያወጣዋል“ እንዲሉ እኔም የተመቸኝ ስለመሆኑ ያን ጊዜ ከጻፉኩት አስተያዬት ዝቅ ብሎ ማንበብ ይቻላል – ከትሁት ምስጋና ጋር። አሁንም በዚህው እቀጥላለሁ። ያቀበለው መላዕክ እንዳለ ስለማምን …. ልኩና ግጥሙም ሥም ነው።
ሀ. ቁምነገር ….
ድርጀት ማለት አንድ ወይንም ከዛ በላይ ያሉ ሰዎች የሚያስማማቸውን ጉዳይ በተሰበሰበ – ፍላጎታቸውን ማዕክል ባደረገ ሁኔታ የሚመሰረቱት የሰዎች ማህበር ነው። ድርጅት ሴቶች በጾታቸው፤ የኃይማኖት ሰዎች በዕምነታቸው፤ ፖለቲከኞች በዓላማቸው፤ ወጣቶች በዕድሚያቸው፤ ሙያተኞች በሙያቸው፤ ሃብታሞች በኢኮኖሚ አቅማቸው፤ የማህበራዊ ኑሮ አድናቂዎች በስሜታቸው፤ የጥበብ ሰዎች በጸጋቸው ዙሪያ ኃይላቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዚያቸውን ፈቅደው በመስጠት ባጸደቁት ወይንምም በደነገጉት ህግጋት ሥር ለመተዳደር የሚፈጥሩት የአቅምና የመንፈስ ጥምር ማዕዶት ነው።
ለእኔ መቼ ተጀመረ ለሚለው ጌታችን መዳህኒታችን እዬሱስ ክርስቶስ ለአዳም ከአካሉ ሄዋንን የፈጠረለት ዕለት ድርጀት ተፈጠረ ብዬ አምናለሁ። ከዚህ ስነሳ ጋብቻ የመጀመሪያው የድርጅት ጽንሰ ሃሳብ ተግባራዊ የሆነበት ማህበራዊ ተቋም ነው። ጋብቻ የሁለት ሰዎች ብቻ ሳይሆን የማህበረሰቡ ሁለንትና ውህዳዊ ቅንበር ነውና። ከዚህ ቀጥሎ ሁለተኛው የድርጅት እድገት ምልክት የኖህ መርከብን የድህነት ስበስብ ተቋም ነውም ባይ ነኝ።
obang5
አንድ ዓላማና ግብ ያለው ድርጅት ሲሆን በዚህ መልክ ከሰው ልጅ እድገት ጋር ድርጀት ከፍ እያለ ሄዶ ዛሬ ካለበት ደረጃ ደርሷል። ሀገር ድርጅት ነው። አኽጉርም ድርጀት ነው፤ ዓለምም ድርጅት ነው። ሀገር ማለት ለእኔ መሬቱ ብቻ ሳይሆን ህዝቡም ነው። ሀገር ማለት በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ዕውቅና ባላው ደንበር የተከለለት መሬት ማለት ሲሆን፤ ህዝብ ማለት ደግሞ በዛ ዕውቅና ባገኘ ክልል ውስጥ ኑሮውን ያደረገ የሰዎች ማህበር ማለት ነው። የሁለቱ ጥምረት ነው የአንድ ሀገርን ምስል ሊሰጠን የሚችለው። አኽጉርም ሆነ ዓለምም ለእኔ የሚሰጠኝ ትርጉም በዚህ መልክ ነው።
በድርጅት ዙሪያ ቅንጅት ሲዊዘርላንድ ሚያዚያ 29.2006 ሲመሰረት ጄኔባ ዩንቨርስቲ አዳራሽ ትቢያዋ ሥርጉተ ሥላሴ አፍ ካለው መቃብር ብቅ ብላ ትንሽዬ ገለጣ ቢጤ አድርጋ ነበር። ያን ጊዜ … ማለት በዕለቱ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ስለ ድርጅታቸው ቅንጅት፤ ዶር አሰፋ ነጋሽ የወያኔ የጤና ፖሊስና ጦሱን በሚመለከት ሰፊ የሆነ ትንተና በመረጃ የተደገፈ ገለጣ አድርገው ነበር።
ከዛ በኋላ ደግሞ ዘርዝር አድርጌ የድርጅት ጽንሰ ሃሳብ፤ ምን ማለት ነው? ድርጀት ምንድን ነው? ድርጀት ለማን? ድርጅት ለምን ያስፈልጋል፤ በጸረ ወያኔ ትግልስ የድርጅት ሚና ምንድን ነው? አፈጻጻም ሂደቱስ በሚል በጸጋዬ ድህረ ገፄ በድምጽ በስፋት ሰርቼው ነበር። ጊዜ ከኖረዎት ጎራ ይበሉና ከክፍል 1 እስከ 6 በዚህ ሊንክ http://www.tsegaye.ethio.info/maedot.html1 ማዳመጥ ስለሚቻል በዝርዝሩ መሄድ አያስፈልግኝም።
ድርጅት ለነፃነት ትግል ገዢ መሬት ነው። እንኳንስ ነፃነትን ለተቀማ ሀገርና ህዝብ ቀርቶ ነፃነት ባለበት ሀገርም የተሰበሰበ የተማከለ፣ የተደራጀ፣ መልክ ዬያዘ ጉዳይ ዓላማና ተግባሩን በሥልጡን – በቅልጡፍ – በታቀደ አኳኋን ለመከወን ከእለት ኑሮ ጀመሮ መንፈስን – አካልን – ፍላጎትን – ራዕይን – ተስፋን – ማደራጀት ለድል ያበቃል። ምርተ – ዝቀሽ – ሰብላማ፤
እንደ እኛ ለአለችች መተንፈሻ ቧንቧዋ በጉልበተኛው ወያኔ ለታፈነ እናት ሀገር ደግሞ ብቸኛው መድህን ነው። አቅምን የመጠነ፤ ኃይልን ያሰባሰበ፤ የሀገርን ልዑላዊነት ያከበረ፤ ከህዝቡ ብሶትና ችግር የተነሳ፤ ወቅቱንና ፍላጎቱን የተረዳ መሪ ድርጅት በጣም ያስፈልገናል። በዚህ ስሌት መደራጅት መብትና ፈቃድ ሆኖ ኢትዮጵያ ላይ ግን፤ ርግጫውና ፍጥጫው፤ ግፊያውና መከራው፤ ባይታዋርነቱና ቅጣቱ የጠነባት ቢሆንም ነፃነትን ፍለጋ የተደራጁ ኃይሎች አሉን። መከራውን ከረመጡ ላይ ሆነው በጸጋ የሚቀበሉ። ውጪ ሀገርም የሀገራችን ጉዳይ ያገባናል፤ ይመለከተናል የሚሉ ወገኖችም በነፃነት ተደረጀተው ትግሉን ተያይዘውታል። አንድ ድርጅት ሲደራጅ በፈለገው ምርጫ ስለሚሆን አደረጃጃቱ የሲቢክስ ወይንም የፖለቲካ ፓርቲ ንቅናቄ ወይንም ግንባር ሊሆኑ ይችላል። ስያሜውም ከፍላጎቱና ከይዘቱ ይመነጫል። obang7
ለ. የሲቢክስ ድርጅቶች መብራት ናቸው ለፖለቲካ ፍላጎቶች ተፈጻሚነት ….
የሲቢክስ ድርጅቶች ገፍተው ከታገሉ የመፍትሄ ቁልፍ ናቸው። ጸጥ ያለውን አብዛኛውን ኃይል የማሰባሰብ አቅማቸው ሙሉዑ ስለሚሆን። የአብዛኛውንም ፈቃድ ስለማይነፈጉ በርካታዎች ሊታደሙባቸው ይችላሉ።። አቻችለው መስመር የማስያዝ ሂደታቸው በአንጻራዊነት የተመቸ ነው። እርግጥ ወገንተኛ ናቸው። ወገንተኝነታቸው ግን በመጫን ሳይሆን አለስልሶ በማቀራረብ። ነፃነት ለአባልተኞቻቸው የመስጠት አቅማቸውም ያልተገደበ ነው። የበታችና የበላይ ግንኙነቱም ቤተሰባዊ ነው። ቢሮክራሲያዊ ነገር ግጥማቸው አይደለም።
በዚህ መሰል ግንዛቤ የሚጓዙ፤ ወይንም ይህ ስሜት የሚማርካቸው የሰዎች ስበስብ ብቻ ሳይሆን ሀገሮችም አሉ ይህን መሰል አቋም የሚያራምዱ። እኔ እንደማስበው ሲዊዝ እንዲህ ያለ ማዕካላዊ ፍላጎትን የማስተናገድ አቅም እንዳላቸው አያለሁ በሀገር ደረጃ።
ምን ለማለት ነው እነዚህ ከፖለቲካ ሥልጣን ዕይታ ባሻገር የተላያዩ የማህበረሰቡን ሙያዊ፤ መክሊታዊ፤ ዕምነታዊ ፍላጎቶችን አስቀድመው የሚነሱ እንቅስቅሴዎች ቅናዊ ዕይታ ከተሰጣቸው፤ ሙሉ ድጋፍና አክብሮት ከተለገሳቸው፤ አዎንታዊ ስሜትን ካልተነፈጉ፤ ለማድምጥ ጆሮ ከተሰጣቸው ለነፃነት ትግሉ ማገር ናቸው። ከስሚንቶ ባላይ የእንቁላል ውሃ ናቸው። ታውቃላችሁ አይደለም የቀደሙ አግናባት በእንቁላል ውሃ እንደሚገነቡ?! በጎንደር ደብረብርሃን ሥላሴ ዙሪያ ያሉት አግናባት የእንቁላል ግንብ ነው የሚባሉት። ውበታቸውም ጥንካሬያቸውም ተፈጥሯዊ ወይንም ኦርጋኒክ ነውና። የሲብኪስ ማህበራት ወይንም ድርጅቶች የሲናሪዎ ችግር ስለሌለባቸው ለአባላቶቻቸው ሆነ ለደጋፊያቸው እንዲሁም ለአድናቂዎቻው ቅርብ ናቸው። ፕሮቶኮሉ የተሰረዘ ነው። ይህ ደግሞ ኃይለኛ ሞገድ ፈጥሮ ድርጅታቸው መንገድ ጠራጊና ተደማጭ ያደርግላቸዋል። ፍላጎት ለውጤቱ እራሱን ይገብራል ደስ ብሎት ….
ሐ.አብነት!
„የድምጻችን ይሰማ“ የእስልምና ዕምነታዊ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ወደር የለሽ፤ ዓላማውን ጠንቅቆ የተረዳ፤ በአንዲት ቅንጣት መልእክት እልፎችን የማስተዳደር ብቃትና ክህሎትን የተቀዳጀ፤ ማንም ሀገር – ማንም ህዝብ ፈጽሞ ያላገኘው፤ ያላለፈበትም ሥልጡን ብልህ እንቅስቃሴ ነበር። አመራሩ በመሪው ሙሉ ድምጽና ፍላጎት ይለፍ የተሰጠው እጹብ ድንቅ እንቅስቃሴ ነበር። ከሰማይ የተፈቀደልት። ጥበቃም የተደረገለት። እጅግ ረቂቅ ፍጹም ድርጊትን የታጠቀ፤ መደማመጠን ያነገሰ፤ ልዑቅ እንቅስቃሴ ነበር። ፍቅሩ፣ መምህርነቱ፣ ተስፋነቱ፣ ብርሃናማነቱ መሆኑ ብቻ ሳይሆን የማይጠፋ … ዘላለማዊ ጧፍ …. ነው። ኢትዮጵዊነትን በአግባቡ በተግባር የተረጎመ። የእንቅስቃሴው ጸሐዮች በሀር ውስጥም ሆነ በውጭ ደግሞ ሴቶች …. ነበሩ። እንዴት እንደምወዳቸው …. አትጠይቁኝ። ትንግርት!
„የድምፃችን ይሰማ“ እንቅስቃሴ አሁን እንኳን ይህ ሁሉ ፈተና በሀገር ውስጡም በውጭም በቀንዳሙ ወያኔም በስፋት እዬተፈተነ ነጥሮ በመውጣት ድንግልናውን በጥር 24.2014 እኤአ በድጋሚ አስመስክሯል። የሰሞናቱ ድንቅ ተግባር የተስፋ ሰብላማ ማህደር አድርጎታል። ታምርና ገድል ነው ለዘመኑ። ለሰላማዊ ትግል የማይደክም ድንቅ ተቋም።
ቀደም ባለው ጊዜ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበር፤ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ማህበር ሆነ አንጋፋው የመምህራን ማህበር በሀገራችን ወሳኝ ድህነታዊ ጉዞ የበቃ ተግባር ፈጽመው ነበር። የዛሬን አያድርገውና በወያኔ ለጠፍ ተሸበበ። የሚተጉ ወገኖች መኖራቸው ሳይዘለል ….
ከዚህ አንጻር ነው ሰፊ ጊዜ ሰጥተን ሞቅ ያለውን ተስፋችን በማረተ ማጭድ ሸክም የሚጭኑ አገላለጾች አግባብነታቸውን እንደ አለ በግልቡ ሳይሆን፤ ፊት ለፊታችን ቁጭ አድርገን፤ በአግባቡ ፈትሸን በደሙ ውስጥ ያለውን መርዝ ማስወጣት አስፈለጊ የሆነው። በዓይን ቀልድ የለምና! በትርጓሜ አቃንቶ መስመሩን መሳተከከል የእያንዳንዳችን መሰረታዊ ተግባር ሊሆን ይጋባል። ቀላል የትም አይደርስ ብሎ ማለፍ ኃላፊነት የጎደለው ጉዞ ነው ለእኔ – ለሥርጉተ።
„ እኛ ስንወለድ ዕምነት አልነበረንም፤ እኛ ስንወለድ ሃይማኖት አልነበረንም … እኛ ስንወለድ ጎሳ እልነበረንም “ ይህን መድህን ቃል፤ ይህን የህይወት ቃል፤ ይህን አጽናኝ ቃል፤ ይህን ቅዱስ መንፈስ የረበበት ቃል ባለፈው ሳምንት „የእኛ ነገር የተሸነፈ ርዕዮትና ሀገር ..“ በሚል ማገደኛው ተክሌ በጻፈው ጹሑፉ ላይ አንዲት ነጠላ ስሜትን ብቻ ለማጣቀሻ ወስዶ ….. “በኢትዮጵያዊነታችን ያጣነው ነገር ስላለ ብቻ ኢትዮጵያዊነታችን ይሰረዛል ማለት አይደለም”። ከባዕድ ስሜት ጋርም አዳብሎ ያስነበበን። ለዛውም ከጃዋርያን ጋር …. ማህጸንን ደም ያስለቅሳል ….
እኔ ዶር. ኦባንግ ኢትዮጵያ ነው የምለው። ዛሬ አይደለም እንዲህ ብዬ የምጠራው ከአምስት ዓመት በፊት እሱ በሚያደርጋቸው ንግግሮች ሥር የምጽፍቸው አስተያቶች ላይ ነበር። እርሰዎም አልለውም። ለምን አርቀዋለሁ? ለመንፈሴ ጥግ ነው። ከስሜቴ ውስጥ እኮ ነው ያለው። አምላኬን ፈጣሪዬን ቅዱስ እግዚአብሄርን አንተ ነው የምለው። አንተ ቅዱስ ገብርኤል እባክህን እርዳኝም እለዋለሁ። እናቴ ቅድስት ድንግል ማርያምንም ከሴቶች የተለዬች ሆና አንቺ እላታለሁኝ። ዶር ኦባንግንም አንተ ስለው በውስጤ አስቀምጬ ነው።
ዶር ኦባንግ ኢትዮጵያ ለእኔ ጠያቂ ነው። የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ስንጠፋበት የት ጠፋችሁ? ምን ልርዳችሁ? ብሎ የሚጠይቅ መንፈሳችን ነው። በ2012 የካቲት ላይ „ጠፋሽ“ ሲለኝ ጉልበተኞች ጠቀጠቁኝ መሸሸግ አለብኝ ስለው „ እኔ እታዘዝሻለሁ አለኝ። እባክሽን አብረሽን ሥሪ“ ነበር ያለኝ። እንደ እኔ በጣም በብዙ ሰው በውስጥ የተቀመጠ ሰው ቢኖር ዶር. ኦባንግ ነው። ግን ተመስጥሮ ነው።
መንፈሳችን የገዛው ጥሩ አያያዙ ነው። ጹሑፎቹ ሁሉ መጨረሻ ላይ የእግዚአብሄር ቃል አለበት። ፈጣሪውን ቅርቡ አድርጎ እያማከረ፣ ፈቃድም እዬጠዬቀ ነው ለነፃነታችን ታግሎ እያታገለን ያለው። ሰላም ፍቅር ምህረትን እያወጀ ህሊናው የታወረው ወያኔ በአሸባሪነት ወንጅሎ የፈረደበት ብርቅዬ የሰው ሰዋችን ነው። እንሱን እንኳን ተዉ እያለ ይመከራል፤ የአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ፕሬዚዳንት ሁላችንንም በፍቅር ለመቀበል ለማስተናገድ የተዘጋጀ ነው።
በማናቸውም ጊዜ ሌት ይሁን ቀን እንደ እኔ ካለች ትቢያ እሰከ ሊቃናት ድረስ ደውለው ያገኙታል። ይህ ስደት ላይ ለምንኖር ለእኛ ለግፉዕና፤ በተለይም ለሴት የነፃነት ትግሉ ቤተኛ እጅግ አስፈላጊና መዳህኒት መንገድ ነው። እኔ በራሴ ስላማወቀው። ይህ የብዕረ -ሞገደኛው መንገድ ኢትዮጵያ በድላሻለች፣ ዝመችባት፣ ጦርነት እወጂባት፣ ምንሽ ናት፣ ግፊያት በአማራ ቆዳ በተዋህዶ መንፈስ የተጠቀለለች በሚል ቄንጠኛ ስሜትን በሚያቀጣጥል …. አቁስሎ ቁስልን እዬቀረፈፉ እንዲደማ፤ መግል እንዲቋጥር የሚያደርግ ነው። ለምን የጃውርን መንፈስ ከኦባንግ ጋር ማገናኘት እንደፈለገ ባይገባኝም ተወን ማለት አለብን። ይህ ወደ ዶር ኦባንግንም ኮተት ማለቱን እኔ የማዬው በዋዛ አይደለም። እም! …. የተላዬዬ ሃሳብ ሰንቃ ስታባትለን የከረመችው ብዕሩ … ስንት ቦታ በወጀብ ስታስመታ ባጅታ አሁን ደግሞ መርዝ መጋዝን …. ልትከዝንን። እእ! አይቻልም። እንብኝ! አ ሻም! አታምሪም እንበላት …. እናትን መጋፋት እንዴት? አኮ!
ዶር ኦባንግ ኢትዮጵያ …ጥቅምት 12.2013 ሲዊዘርላንድ ዙሪክ መጥቶ ነበር። የጋባዙት የአዲሱ ትውልድ ቅዱስ መንፈስ ያላቸው የወጣቶች የሰብዕዊ መብት ድርጅት ነበር … በምን ቋንቋ በምን ቃላት በምን ዜማ የስበሰባው ታዳሚዎችን ስሜት ልግለጽላችሁ ……..
እሱን ስናይ፣ እሱን ስናገኝ፣ እሱን ስናደምጥ፣ ድህነትን ሲያውጅ ቂም በቀልን ሲያወግዝ “ወገኖቼ ከወያኔም እኮ ጥሩዎች አሉ አስኪ ምርመሩት” ሲለን … አዬ አንተ ትሩ ሰው። የተዘጋጀለትን የክብር ቦታውን ትቶ መጥቶ ነበር ከ እኛ ጋር የተቀመጠው። ከአጠገቡ ለመቀመጥ ሽሚያ ነበር …
እስራኤል ላይም በነበረው ቆይታው … ወጣት የትግራይ ልጆች ስሰባውን ጠቅጥቀው ሲወጡ “የእኛ ትግል እናንተንም ነፃ ለማውጣት ነው” ነበር ያላቸው።
እጅግ የማከብራችሁ የሀገሬ ልጆች … ካለ እንደዚህ ዓይነት ፈውሶች እንደ በደላችን እንጨራረሳለን። ወያኔ አቁስሎናልና ወያኔ ሲለቅ፤ በቀል ተጠምቆ መጨፋጨፍ አይቀሬ ነው። ግን እንደ ዶር ኦባንግ ያለ …. እንደ ጋዜጠኛ አብርኃም ደስታ ዓይነት ወጣቶችን ንጹህ መንፈስ ጥሶ የሚሄድ ሞራልም ተፈጥሮም የኢትዮጵያዊነት ጨዋነት የለም። …. ይህ ሚስጢር ነው ለተፈቀደላቸው ብቻ የሚገልጽ። እስራኤል ላይ ፈልቶ የነበረውን ስሜት አብርዶ፤ አስታግሶ ወጣቶቹ አብዛኞቹ ተምልሰው ከወገናቸው ጋር ታዳሙ በኢትዮጵያዊነት፤ በዛ ድንቅ የወል ማራኪ መንፈስ „….. አቶ መለስ የሚነዳው ባቡር የጥላቻ ባቡር ነው…..አሁን ባቡሩ እየቆመ ነው” በ25.06.2013 እስራኤል ከተደረገው ንግግር የተወሰደ።
ሲከፋን ብቸኝነት ሲያለፋን፤ ዙሪያ ገባው ሲጨልምብን የወገን ነገር ሲቆጠቁጠን፤ እረፍት ሲነሳን መተንፈሻ ቧንቧ እሱ ነው።
እኔ የሳውዲ ችግር ሲመጣ ወዲያውኑ ነበር የደወልኩለት። አሞት ነበር፤ ግን ሥራ እንደ ተጀመረ ሲነግረኝ ተገስ አለልኝ። ሰው እኮ ነን፤ ማሽን አይደለንም። የፈለገ ጠንካራ ብንሆንም አንድ አጽናኝ ያስፈልገናል። “አንድ ዓይን ቢኖራት እሱንም በዘነዘና” እንዳይሆን ሃብቶቻችን በጥንቃቄ ልንይዝ ይገባል። እንዲህ ዓይነት መንፈስ ያለው ሰው በ100 ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው የሚፈጠረው። ለነገሩ እኛ ማድነቅም ማመስገንም ሆነ በቅን ዓይን ማዬትም አይሆንልንም። … ተበድለናል ይመስለኛል። ይህም ሆኖ ደግሞ ተስፋችን ላይ ዲዲቲ መነስነስ አይፈቀደም። ….. http://freedom4ethiopian.wordpress.com/2013/06/page/8/
ዶር ኦባንግ …. ስለ ሴቶችም ቀና አመለካከት ነው አለው …. ያለንን ተዝቆ የማያልቅ አቅምና ዕምቅ ጥሪት አሳምሮ ያውቃል …. የማረተ ማጭድ ሊያሸክመን የፈለገውን ጠቀራ ማሸቀንጠሪያችን ሌላው ድንቅ ገለጻ ….
“(መጋቢት 7 ቀን 2004 ዓ.ም. March 16, 2012)፦ የአገራችን ግማሽ ህዝብ የሚሆኑትን ሴት እህቶቻችን ያልተሳተፉበት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ምስረታ ስኬቱ ያማረ እንደማይሆን፣ ቢሆንም ራሱን ለጥፋት እንደሚያጋልጥ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ተናገሩ።“አገራችን ሁሉም ዓይነት ሴቶች ያስፈልጓታል። አምላክ ለዚህ የተቀደሰ ተግባር የጠራው የተማሩትንና የተሻሉትን ብቻ አይደለም። ሁሉንም እንጂ! ስለዚህም በኦሞ ሸለቆ ከንፈሮቿ ላይ ሸክላ ከምታንጠለጥለው ውብ ጀምሮ በአዲስ አበባ ከንፈሮቿን ቀይ ቀለም እስከተቀባችው ቆንጆ፤ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ባዶ እግሯን ከተዋበችው ጀምሮ በዋንዳቢቲ እስካጌጠችው የኦሮሞ ኮረዳ፤ በኦጋዴን በሒጃብ ካሸበረቀችው ኢትዮጵያዊት ጀምሮ ባማረ ጥለት እስከተዋበችው የአማራ ቆንጆ፤ ግማሽ አካሏ እርቃን ከሆነው የአፋር ድንቅ ጀምሮ በሹርባዋ እስከተዋበችው የትግራይ ሴት … ሁሉም ዓይነት ሴቶች ኢትዮጵያችን ያስፈልጓታል።” ሲሉ አቶ ኦባንግ ተናግረዋል።
http://ethiopiazare.com/the-news/2236-obang-speech-to-ewccc-conf
መ..ዶር. ኦባንግ ኢትዮጵያ ለወገኖቹ ትልቅ ጆሮ አለው በፍቅር የማዳመጫ፤ ኖሮይ ላይስ? …. ኦባንግ ሜቶ በተጋባዥነት የተገኙበት ይህ ውይይት ሲጀመር የማህበሩ ሊቀመንበር ወ/ሮ ዙፋን አማረ “ውድ ወንድማችን፣ ውድ የኢትዮጵያ ልጅ፣ኢትዮጵያዊያን ርዳታ በጠየቁበት ሁሉ ጊዜ፣ ገንዘብ፣ የቦታ ርዝማኔ ሳያግድህ ፈጥነህ ትደርሳለህና ሁላችንም ላንተ ታላቅ አክብሮት አለን” አሉ። ኦባንግ መድረኩን ተረክበው “የማደርገው ሁሉ ለህሊናዬና ነው። ማድረግ የሚገባኝን አደርጋለሁ። ግዳጄም ነው። ምስጋና አያስፈልግም ዛሬ ንግግር ሳይሆን ምክር እሰነዝራለሁ” የሚል ምላሽ ሰጡና ስለ መደራጀት፣አበክረው፤ተናገሩ።
“አማራጭ ቢኖረን ስደትን አንመርጥም ነበር። በአገራችን ግፍ ባይፈጸምብን ኖሮ አገራችን እንኖር ነበር”
https://www.facebook.com/ethionewss/posts/373710216047710
በ2009 እ.ኤ.አ አንድ ዓለምአቀፍ የ የኢትዮጵያውያን የጋራ አሜሪካን ሀገር ስበስባ ነበር። ከርንት አፊረስ ላይ በቀጥታ ይተላለፍም ነበር። ቀኑን አላስተወስውም ከዛ ላይ የሴቶች ተወካይ ዶር አበባ ተገኝተው ነበር። የሚናገሩት ከዶር ኦባንግ ቀጥለው ነበር። እንዲህም አሉ። ” እኔ በኦባንግ ንግግር በጥልቀት ተመስጬ ስለነበር ልናገር ያስብኩትን ሁሉ እረስቼዋለሁ። በጣም ነበር ስሜቴን የገዛው። ከዚህ በላይ መናገር አልችልም፡” ሴቶች ይህን ወንድም በምን መልኩ አዬት? እናት ባላት ጥልቅ ጸጋ ተረጎሙት።
ለማሰረጊያ በ2013 የተገኘው ድንቅ ፍሬ ….
በሀገረ አሜሪካ ታላቅ የምክክር ሸንጎ ከሹሞች ጋር “ኢትዮጵያና ድሕረ መለስ” ስለወገኖቹ ስለ ነፃነት ጥማታችን ዶር ኦባንግ ምን ተናገረ …“ህወሓት እስካሁን በነጻ አውጪ ስም አገር እየመራ እንደሆነ፤ መለስ ለህዝባቸው “ሬት” ለምዕራባውያንና “ማር” (የቤት ቀጋ፤ የውጭ አልጋ) ዓይነት መሪ እንደነበሩና የኢትዮጵያ ሕዝብ ላለፉት 22ዓመታት በመከራ ውስጥ ያለና የዛሬ 8ዓመት በዚሁ ቦታ ላይ ያማሞቶ ኢትዮጵያ በአቋራጭ መንገድ (ክሮስሮድ) ላይ እንደምትገኝ” መናገሩ አቶ ኦባንግ ካስታወሱ በኋላ “መቼ ነው መንገዱን የምናቋርጠው? ከስምንት ዓመት በኋላ አሁም አንሻገርም ወይ፤ አናቋርጠውም ወይ” በማለት ተሰብሳቢውን ያስደመመ ለሰብሳቢዎቹ ግልጽ ጥያቄ ጠይቀዋል፡፡
አቶ ኦባንግ ሲቀጥሉም “ኢትዮጵያውያን የምንጠይቀው በጣም ቀላል ጥያቄ ነው፤ አሜሪካኖች የሚመኩበትን ሰብዓዊ መብት እኛ ተነፍገናል፤ ..” አሜሪካኖች ነጻ እንድታወጡን አንጠይቃችሁም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ነጻ እንደሚወጣ ያውቃል። እናንተ ግን በነጻነት መንገዳችን ላይ ዕንቅፋት አትሁኑብን፤ (የነጻነት መንገዱን አትዝጉብን)። ከመንገዱ ላይ ገለል በሉ … እስካሁን ያልተሞከረ መንገድ አለ … እሱም እርቅ ነው … ከመንግሥትም ሆነ ከተቃዋሚው በኩል ዓመኔታ የሚጣልባቸው አሉ … ” አቶ ኦባንግ ሜቶ፡፡ http://www.goolgule.com/ethiopia-after-meles/
የእኔ ጌጦች ይህን አልማዝ ያመረተ ህሊና ኢትዮጵያዊነትን የሰበከ አንደበት ታሪክና ትውልድን፤ ዕመነትንና መከባበርን፤ ፍቅርና ናፍቆትን፤ ፍልቅ ስሜትና ተስፋን ለነገ ያጫ፤ ለዛም ቀን ተሌት በተጠራበት ቦታ ሁሉ አቤት ወዴት ብሎ የሚታዘዝን መንፈስ ነው ከጃዋርውያን ጋር አዳቅሎ አቶ ሞገደኛው ያቀረበው። ስለሆነም እዬተስተዋለ በጥንቃቄ ይምርምር እንላላን እኔና ብዕሬ። በሉ እንግዲህ … የነጠረውን ፍርድና ዳኝነት ከጨዋውና ሚዛን ከሆነው ወገኖቼ ንዑድ መንፈስ ውስጥ አስቀምጬ እኔ በለመደ እጄ በሌላ ጉዳይ ዙሪያ ከች እስክል ድረስ ሞቅ ደመቅ ባለ ፍቅር፤ በዘንካታው ኢትዮጵያዊ ትህትና እሰናበታለሁ። ደህና ሁኑሉኝ …. የኔዎቹ መንፈሶቼ።
• ማሳሰቢያ ዛሬ ማገናዘቢያ ሊንኮች በርከት ብለዋል። የግድ ነበር። ነገን ሲታሰብ ከተቻለ በተሟላ መረጃ መሆኑ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊም ነው። ሰው ቋሚ አይደለም …. ጊዜም፤ ከተረት ተረትም መዳንም ይቻላል።
• የሀገረ እስራኤል ወገኖቻችን ፎቶ ከከረነት አፊረስ ድህረ ገጽ፤ የዶር ኦባንግ ከጎልጉል፤ የሲወዝ ፎቶ ከእኛው ቤት፤
“ከጎሳ ይልቅ ለሰብዕዊነት ቅድሚያ እንስጥ!” የአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መሪ ቃል ።
እግዚአብሄር አምላክ ኢትዮጵያዊነትን ከሚዋጋ ጠላታዊ ስሜት ያድነን! አሜን!
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments:

Post a Comment