Monday, December 9, 2013

የአፄ ምኒልክ 100 ኛ ሙት-ዓመትና ክንዋኔዎቻቸው


አውሮፓውያን ከዚያ በፊት ያልታዬ ከእርስ -በርስ አስከፊ ፍጅት የደረሱበት የአንደኛው የዓለም ጦርነት ሊፈነዳ 7 ወራት ገደማ ሲቀሩት ነበረ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ታኅሳስ 3 ቀን 1906 ዓ ም ያረፉት።
በዘመኑ ብቸኛይቱን አፍሪቃዊት ነጻ ሀገር ይመሩ የነበሩት አፄ ምኒልክ ህዝባቸውና የጦር አለቆቻቸውን አስተባብረው ፣ መላ ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ሥር ለማድረግ የዘመተውን የኢጣልያ ጦር ኃይል አድዋ ላይ ድል በመምታት ፣ በዘመኑም የዘመናዊ ሥልጣኔ መገለጫዎች የነበሩ ስልክና ባቡር ሐዲድ በማስገባት ፣ ት/ቤትና ባንክ የመሳሰሉትን ተቋማት በመክፈት ይታወቃሉ። በውጭው ዓለም የተፈሩ ፣ የተከበሩ ፣ በቅኝ ግዛት ሥር ለነበሩ አፍሪቃውያንና ከባህር ማዶ ፣ በካሪቢያን ደሴቶችና በሰሜን አሜሪካ፣ ለአፍሪቃ ዝርዮች እንደ ነጻነት አባት፤ ሀገራቸውም የጥቁር ህዝብ አለኝታ ሆና ትታይ ነበር። ከጦርነት ይልቅ፤ ውዝግቦችን በሰላም፤ በዘዴ ፣ መፍታትን ይመርጡ የነበሩት ንጉሠ-ነገሥት፣ ሉዓላዊ ግዛት በመመሥረቱ ረገድ፣ በዓለም ታሪክ ውስጥ የተለዬ ነገር ባያደርጉም፤ ካረፉ ከ 100 ዓመታት ወዲህም፣ ብዙዎች የሚወዷቸውንና የሚያደንቋቸውን ያክል የሚወቅሷቸውና የሚከሷቸውም አሉ። አጼ ምኒልክና ክንዋኔዎቻቸው በታሪክ እንዴት ይመዘናሉ?በዛሬው እንወያይ፣ የዳግማዊ አፄ ምኒልክን 100ኛ ሙት ዓመት መነሻ በማድረግ፤ ክንዋኔዎቻቸውን ፤ ውርሳቸውን በአጭሩ እንቃኛለን። 3 እንግዶች ጋብዘናል።
ተክሌ የኋላ
ልደት አበበ

dw.de

No comments:

Post a Comment