Tuesday, December 24, 2013

ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን! “ከ 40 ግድብ አንድ የአሰብ ወደብ” – ከሰመረ አለሙ


ኤርትራዉያኖች ተበልጠዉ በኢትዮጵያ ተንደላቅቀዉ የሚኖሩበትን ሁኔታ ከተነጠቁ በሗላ እንደገና እጃቸዉ ለማስገባት በተለያየ ዘዴ ቢጠቀሙም ህዋአት እና ሻቢያ “እባብ ለባብ ይተያያል ካብ ለካብ” አይነት ሆነና ኤርትራዉያን የፈለጉትን ያህል ሳይሆንላቸዉ ቀርቶ እዚሀ ላይ ተደረሷል። የጸሀየ ግብአተ መሬት ፉከራ ከከሸፈ በሗላ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያን ሊበትንልን ይችላል የሚሉትን ሀይል እና ዘዴ ቢበደሩም መላ ቢመቱም ቢያሰባስቡ እና ቢያሰለጥኑም፤ የኢትዮጵያ አንድነት ፍንክች ሳይል ቀርቶ እዚህ ላይ ይገኛል። የኤርትራ ምሁራን ኢትዮጵያ ያስተማረቻቸዉ ተራ ወርደዉ የሚያስገምት ጽሁፍ ቢጽፉም፤ በቀይ ባህር ማተሚያ ቤት የእዉሸት ፋብሪካቸዉ ተረት መሰል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢያሳትሙም፤ ቅጥፈት የተሞላዉ ወረቀት ቢጽፉም ድካማቸዉ ሁሉ ያለምንም ፍሬ ልፋት ብቻ ሁኖ ቀርቷል
ታድያ ለሁሉም ብልሀት አለዉ እንዲሉ ይህ ዘዴ ያለመስራቱን የተረዱ ኤርትራዉያን አቶ መለስንና ለኤርትራ ስስ ልብ ያላቸዉን የህወአት ባለስልጣኖች በመጠቀም ዛሬም ከዜጋዉ በላይ የኢትዮጵያን በረከት እየተጎናጸፉ ይገኛሉ። በተለይ ከአቦይ ስብሀት አለንላችሁ መግለጫ በሗላ ብዙ ኤርትራዉያን ባላቸዉ ንክኪ አማካኝነት በብዛት ወደ ሀገር ጎርፈዋል ከኢትዮጵያ ሳይባረሩ የቀሩትን ወገኖቻቸዉንና በዉጭ ሀገር በሚኖሩ ኤርትራዉያን አማካይነት የዉስጥ ለዉስጥ ግንኙነታቸዉን በማጠናከር ኢትዮጵያ ዉስጥ የቀድሞ ቦታቸዉን ይዘዋል።
በቅርቡ በወጣዉ ጽሁፍ ወደ 1700 የሚሆኑ የኤርትራ ተወላጆች ከኢትዮጵያዉያን ወጣቶች በላይ ቅድሚያ ተሰጥቷቸዉ ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ጎርፈዋል ይህ አፊሲያላዊ ቁጥር ነዉ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ ቁጥር እንዳላቸዉ እማኝነት ያላቸዉ ዜጎች በቁጭት ይገልጻሉ። እንግዲህ ልብ ይበሉ እንደ አይን ብሌን በምናያቸዉ የትምህርት ተቋማት ኢትዮጵያዊዉ ወጣት በጫት የቀን ህልም ሲያልም ትላንት ኢትዮጵያ ላይ የተኮሱ ዛሬም ለኢትዮጵያ ክብር እና ፍቅር የሌላቸዉ ኤርትራዉያን በኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ሲማሩ በእጂጉ ያሳዝናል።እነሱ እንዲማሩ ሌላዉ ኢትዮጵያዊዉ ቦታዉን ለነሱ መልቀቅ አለበት ማለት ነዉ።
ethiopias-planned-renaissance-damይህ በትምህርት ዘርፍ የተገኘዉ መረጃ ነዉ። በንግድ፤እርሻ፤ፐሮፐርቲን በተመለከተ ከሀገሬዉ ነዋሪ በላይ እዛ ያሉትም ከኤርትራ፤ከአዉሮፓ እና አሚሪካ እየጎረፉም በከፍተኛ ሁኔታ በመጠቀም፤በመጠቃቀም፤ከባንክ በመበደር እና በማምታት ህገ ወጥ ጥቅም በማግኘት ላይ ይገኛሉ። ገንዘብ ማሸጋገር ዋናዉ አገር መጉጃቸዉ ነዉ በዚህም ሂደት ገንዘብ አገሩን እየለቀቀ በባህር ማዶ ባንክ እና በዉጭ ሀገር ኢንቨስትመንት ላይ ይዉላል። እነሱም በዚህ ህገ ወጥ ስራ አንድም ጠላታቸዉ ኢትዮጵያን ይጎዳሉ አንድም ትርፋቸዉን ያደልባሉ። በህጋዊ መንገድ ቀረጥ ከፍለዉ ከመስራት ይልቅ ህገወጥ የሆነዉ መንገድ ባያተርፋቸዉም ይመርጡታል።
የሚያሳዝነዉና አንጀት የሚያበግነዉ እኛዉ መሀል ስንት ቤት ሰርተሀል? ሰሞኑን ምን ልከሀል? ትንሺ ገንዘብ ሰጥተህ በትግራይ በኩል ዘመድህን አስመጣ እያሉ በድፍረት ሲያወሩ በጣም ልብ ይሰብራል። ይህች ሀገር መች ነዉ ለዜጎቿ የምትሆነዉ? መች ነዉ ዜጎቿን የምታከብረዉ? መች ነዉ ዜጋዉ ከእንደዚህ አይነት ጥቃት ድኖ ሀገሩ የእርሱ መሆኑን የሚረዳዉ ብዬ አንዳንዴ እራሴን እጠይቃለሁ። እንደዉም ደግሞ የድፍረት ድፍረት ከህዋአት ጭቆናም ነጻም የሚያወጡን እነሱ ሁነዉ ተገኝተዋል ጆሮ የማይሰማዉ የለ። የአለሙ ሚዲያ አምነስቲ ኢንትርናሽናልን ጨምሮ በወር 3000 ኤርትራዊ አገሩን ይለቃል ሲባል አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ከህዝቡ ፍቅር የተነሳ ያለ አጃቢ ነዉ የሚሄዱት ብለዉ ተቃዋሚዎቻችንን ሊያሳምኑን ይከጂላቸዋል ታዲያ ይህ ሁሉ ፍልሰት ነጻነት ፍለጋ ካልሆነ ፍለሰቱ አድቬንቸር ነዉ ማለት ነዉ ወይስ አቶ መለስ እንዳሉት ኤርትራዉያን እግር እንጂ አገር የላቸዉም የሚባለዉ አባባል እዉነት ሊሆን ነዉ?
በመሰረቱ አፍቃሪ ኢትዮጵያ ኤርትራዉያን ኢትዮጵያ ዉስጥ መኖራቸዉ ቅር የሚለኝ ሰዉ አይደለሁም ባለፈዉ ጽሁፌም እንደገለጽኩት ሀገሪቱ ዛሬ በስልጣን ላይ ቁጭ ብለዉ ከገደሏት በላይ ለሀገራቸዉ ኢትዮጵያም የሞቱ ታላላቅ የኤርትራ ተወላጆችንም ገልጫለሁ ምንም እንኳን ዛሬ በህይወት ባይኖሩም ለነሱ ያለኝ አድናቆትና ክብር ከጊዜዉ ጋር የሚደበዝዝ አይሆንም። እኔም የምኖረዉ በዉጭ ሀገር ነዉ ልዩነቱ እኔ ዛሬ የምኖርበትን ሀገር በክብር እና በፍቅር የማገለግል ነኝ በሀገሩ ተጠቃሚ ሁኜ ለሀገሩ ጥፋት የምመኝ አይደለሁም። ይህ ነዉ የእኔና የዘመኑ ኤርትራዉያን ልዩነት።
ዛሬ ሰዉ ምን ይለኛልም ቀርቶ ኤርትራዉያን በግላጭ ኢትዮጵያ የጋራችን ኤርትራ የግላችን፤ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ የሚል ፌዝ የሚመስል ፌዝ ያልሆነ ቋንቋ በብዛት ሲጠቀሙ ይሰተዋላሉ። የሚገርመዉ ሀገር ዉስጥ ኑሮዉን ዘርግቶ የሚገኘዉ ኤርትራዊ ወይም ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ በፍልሰት የሚገባዉ ኤርትራዊ ስለ አሰብ ምን ታስባለህ ስለ ባድሜ ምን ታስባለህ ተብሎ ቢጠየቅ መልሱ ለማያዉቃት፤ ላልኖረባት ፤ ላልተጠቀመባት፤ ለተንገላታባት አገሩ ኤርትራ ነዉ።
ኤርትራዉያን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዉያን ሰፈር እንዴት ተንሸራተዉ እንደገቡ ግንዛቤ ቢያስፈልግ አንድም የህዋት ንክኪያቸዉን በመጠቀም፤ማንነታቸዉን በመለወጥ ሲሆን ሌላዉ ደግሞ በግንዛቤ የተጎዳዉን ኢትዮጵያዊ እየመረጡ በመጠቀም ነዉ። አንበሳዉ አለማየሁ መሰለንማ ማን ይደፍረዋል ተጠቃሚዉን ይጠቀምበታል እንጂ። እንግዲህ ወደፊት በስፋት ብመለስበትም ጀግና በጠፋበት ዘመን እንደ ቀድሞቹ ጀግኖች አያቶቹ በጠላት ሜዳ ተረማምዶ ግዳይ ጥሎ የቁርጥ ቀን ሲመጣ ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት እንደሆነ አስመስክሮ ኢትዮጵያዉያን ሰፈር እንደገና የተሀድሶ መንፈስ ለሰጠዉ አለማየሁ መሰለ በያለንበት ዋንጫችንን እንድናነሳ በትህትና እጠይቃለሁ ገድሉም ከጊዜዉ ጋር ሊደበዝዝ አይገባም። በእዉነቱ አለማየሁ ያነን የመሰል ገድል ሲሰራ ዉቅያኖስ ጠልቆ ዉሀ ሳይነካዉ እንደወጣ ዋናተኛ ነዉ የምቆጥረዉ። ከጀብድ ስራዉ በላይ ደግሞ ንግግሩ የቀድሞዎቹ አንበሶች አያቶቹን መንፈስ የሚያንጸባርቅ ነበር። አለማየሁ በአንድ ቃለ መጠይቅ “ተስፋዬ ምንም እንኳን የሻቢያ ሰላይ ቢሆንም እኛም ከእሱ በላይ መስራት እንችላለን በሚል ጽኑ ኢትዮጵያዊ መንፈስ ስራዬን ተያያዝኩት” ነበር ያለዉ። ቆፍጣናዉ አለማየሁ በእዉነት የዘመናችን በላይ ዘለቀ ቢባል ብዙም ማጋነን አይሆንም ሰዉ የሚለካዉ እንደየዘመኑ ነዉና።
ኢትዮጵያ ጥንታዊ እና ገናና አገር ነች በዚህ በረጂም ዘመኗ ረጅም ስርን ተክላለች በረጂም ዘመኗም ብዙ ጠቃሚ እዉቀቶችን፤እምነቶችን፤መረጃዎችን ለዜጎቿ እና ለአለም አበርክታለች ከዚህ እና ከሌላም ስንነሳ ኢትዮጵያ እንደሀገር ኢትዮጵያዉያንም እንደተከበረ ዜጋ በቀጣይነት መኖር አለባቸዉ። ኢትዮጵያ ትላንት በግርግር እንደተፈጠረች ሁሉ አንዳንድ ብሄረተኞች አንድም የበታችነት መንፈስ በተጠናወታቸዉ በሌላም በባእድ ሀይሎች እየተገፉ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉያንን ለመፈታተን የሚያደርጉት ጥረት ያለ ይሉኝታ ሊመከት ይገባል እላለሁ።
እንግዲህ እንዲህ ያለዉን አልፎ ሂያጅ የግርግር መንፈስ ሳይበግረዉ በእዉቀቱ ስዩም እንዳለዉ ወጣቱ ኢትዮጵያ አገሩን ከአባቶቹ በበለጠ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ማድረስ ይገባዋል እላለሁ። ዛሬ እንዲህ አደርግልሀለሁ እንዲህ ብናደርግ የምድር መንግስተ ሰማያት እንኖራለን በሚል ቀቢጸ ተስፋ የሰፈሮቻቸዉን ልጆች እያማለሉ ኢትዮጵያዊነት ላይ ወገኖችን የሚያስኮርፉ ነገ ሀሳባቸዉ ተሟልቶ እነሱ ኢትዮጵያን ቢከፋፈሉ እንደ ደሀ አጥር ሁሉም እየጣሳቸዉ ይሄዳል እንጂ እነሱም ተጠቃሚ እንደማይሆኑ በልምምጥ ሳይሆን በድፍረት ሊነገራቸዉ ይገባል። ፍቅርን የሚያዉቅ ጀግና ብቻ ነዉ እነሱ ግን ፍቅርን ልምምጥ ያደርጉታል። እነሱን ትልቅ ያደረገ እንዲህ የማኩረፍ ነጻነት ሁሉ የሰጣቸዉ ኢትዮጵያዊነት ነዉ። በአንድ ወቅት ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ሐይሌ የዘረኞች እብሪት ሲበዛ አይተዉ ለአንዱ ዘረኛ በሰጡት መልስ ምንሊክ ባይሰበስቡህ እራስህን አንዱ የጎረቤት አገር ታገኝዉ ነበር ያሉት ዛሬም በባዶ ሜዳ ለሚያብዱ ነገር ለጠፋባቸዉ ዘረኞች በግልጽ ሊነገር ይገባል እላለሁ። እነዚህ የምንሊክን ታላቅ ስራ የማያዉቁ ደካሞች ምንሊክ ባይሰበስቧቸዉ ስማቸዉ ሌንጮ/ሀጎስ/ጫላ/ለማ… ከመሆን ይልቅ ሪካርዶ/ሮበርት/ዴቢድ ሲሆን ሀይማኖትም በልካቸዉ ይሰፋላቸዉ ነበር። የሚያሳዝነዉ የፕሮፌሰሩ ጽሁፍ ከግማሽ ቀን በላይ በድረ ገጾች ላይ አልዋለም ምክንያቱም የታወቀ ነበር።
እዚህ ላይ ላልፈዉ የማልፈልገዉ ስለ ታላቁ የኦሮሞ ህዝብ በኢሳይያስ ታግተዉ ጻፉ በሚባሉ ዘረኞች በነ አስመሮም ለገሰና 12ኛ ክፍል ባልጨረሰ መሀይም ተጽፎ ለንባብ ሲበቃ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል ዛሬ በኢትዮጵያ ምስረታ በኢትዮጵያ ስነጥበብ በኢትዮጵያ አስተዳደር የኦሮሞ አሻራ ያላረፈበት አንድም ነገር አይገኝም። በሀገር እና ከሀገር ዉጭ ታላላቅ የኦሮሞ ጠቢባን ባሉበት አለም ስለ ኦሮሞ ህዝብ ታላቅነት፤በደል፤ጭቆና ከኤርትራ ኤክስፖርት ሲደረግ ከምንም በላይ የሚያሳፍረዉና የሚያዋርደዉ የኦሮሞን ህዝብ እንጂ ሌላዉን አይሆንም። የኦሮሞ ህዝብ ሞግዚት የሚያስፈልገዉም አይደለም የኦሮሞ ህዘብ በደሉን እና ጥቅሙን በሚገባ ያገናዝባል የኦሮሞ ህዝብ ህመም ከአማራዉ፤ጉራጌዉ፤ወላይታዉ…. በላይ እነ አስመሮም ለገሰንና ተስፋዬ ገ/አብን ለምን እንዳመማቸዉ ነገሩ ግልጽ ነዉ እነሱን ያቃታቸዉን ሀይል እነሱ እንዲሞክሩላቸዉ ታስቦ ነዉ ታዲያ ኦሮሞ ይህን አጣ? የምን ንቀት ነዉ? ከኦሮሞ እና አማራዉ የተወለደ 10 ሚሊዮን ህዝብ ከመኖሩም በላይ የአንዱን ደም አጥርቶ አንተ ከዚህ ነህ አንተ ከዚያ ነህ የሚያሰኝ ሁኔታም አይኖርም። አሁንም የኦሮሞን ህዝብ አታላግጡበት አርፋችሁ ቁጭ በሉ ሊባሉ ይገባል። ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ምነዉ ተስፋዬ ገ/አብ ከኦሮሞ በላይ ኦሮሞ ሆነ ያሉት እነ አስመሮም ለገሰን አፍ አዘግቶ እዛዉ እስር ቤታቸዉ ሊያስቀምጣቸዉ በቻለ ነበር ታድያ እነሱ ለክብር ስላልተፈጠሩ በተቻላቸዉ መጠን ቶሎ ትርፍ ያመጣልናል ብለዉ የሚሉትን ብቻ መሞከር ስለሆነ ሊማሩ አይችሉም። እንደ እዉነቱ ከሆነ በዛሬዉ አለማችን ከማንም በላይ በባርነት ቀምበር ስር ያለ ህዝብ ቢኖር ኤርተራዊ በመሆኑ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ካማራቸዉ እዛዉ በእስር ቤት የሚኖረዉ ህዝባቸዉንና እራሳቸዉን ነጻ እንዲያወጡ ይጠየቃሉ ለዛም ካልታደሉ ተራ የኢሳይያስ ካድሬ መሆናቸዉ ቀርቶ በክብር እንዲቀመጡ እናሳስባለን 90 ሚሊዮን ህዝብን መናቅ የጤንነት አይመስልም።
ለማጠቃለል በስልጣን ላይ የተቀመጡት ህዋቶች በአቶ መለስ ምንጠራ አክራሪ ትግሬዎች ተነስተዉ በአብዛኛዉ ኤርትራ እና አፍቃሪ ኤርትራዉያን ቦታዉን በመያዛቸዉ የትግራይ ወንድሞቻችን ነገ ከሚመጣዉ ጥፋት እራሳቸዉን ለመከለከል ከወገናቸዉ ጋር ሰልፍ እንዲቆሙ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ። ትላንት የትግራይ ወንድሞቻችንን ነፃ ለማዉጣት፤ የትግራይ ክልል ባድሜ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ድምበሮች እንዲከበሩ በዛ የፈሰሰዉ ደም ከንቱ ሁኖ ቀርቷል። ባድሜም ለኤርትራ ሊመለስ ዉስጥ ለዉስጥ ዲፕሎማሲዉ ተጧጡፏል ኤርትራዉያንም ያለምንም ችግር በኢትዮጵያ የቀድሞ ቦታቸዉን በመያዝ ላይ ናቸዉ። ትላንት የትግራይ ህጻናትን በቦምብ የፈጀ ሀይል ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ወዳጂ የሚያደርገዉ ምንም ነገር ሊኖር አይችልም ህዝቡም አስተዳደሩም ትላንት የነበረ ነዉና። የኢትዮጵያም ህዘብ በችግሩ ጊዜ የችግሩ ተካፋይ ካልሆናችሁ የችግራችሁ ጊዜ ብቻ ድረሱልን ብትሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ደግነቱና እርዳታዉ ቀጣይነት ሊኖረዉ ስለማይችል ካሁኑ ማሰብ አግባብ ነዉ እላለሁ።
እንግዲህ በእነ ገበየሁ ባልቻ፤በላይ ዘለቀ፤በላይ ቃለአብ፤ኡመር ሰመታን፤ታከለ ገ/ሀዋያት፤አብዲሳ አጋ በነ አፈወርቅ ወ/ሰማያት እና ዛሬ ደግሞ እንደ ጎሹ ወልዴን
አለማየሁ መሰለን የመሰሉ ጀግኖቻችን ባሉበት አገር ወገን ዉርድተን መቀበል በእጂጉ ይከብደዋል። እንግዲህ የተኛዉ ወገን ነቃ ብሎ እንዲጠበቅ መሰሪዎችም እንዲጠነቀቁ ያህል ነዉ እንጂ ምን ያልተጻፈ አለ ሰሚ፤ አንባቢና አገናዛቢ ከተገኘ። ይህችን ጽሁፍ ከከተብኩ በሗላ በህዋትና በሻቢያ መሀከል በራቸዉን ዘግተዉ ኢትዮጵያንን አግልለዉ ከዚህ በፊት እንዳደረጉት ሁሉ በተዋራጅነት የሚያስቀምጥ አንዳንድ ድርድሮችን በማድረግ ላይ እንደሆኑ ጠቋሚ ጽሁፎች በብዛት ተሰራጭተዋል። ኤርትራ ኢትዮጵያ ኮሚቴም የሚባል የማወናበጃ ስብስብም በየቦታዉ እንደ አሸን ብቅ በቅ እያለ ነዉ። ብዙ ለግላጋ የኢትዮጵያ ህጻናት ያለቁበት የትግራይ ከልል ባድሜም በተዋራጂነት ለኢሳይያስ አፈወርቅ በእጅ መንሻነት ህዋአት ሊያስረክበዉ እንደሆነ ይገመታል። እንግዲህ ይህንና ሌላዉን አጠቃለን ስንመለከተዉ ኳሷ ያለችዉ የትግራይ ወንድሞቻችንን ክልል ስለ ሆነ ወደ ወገናቸዉ ተጠግተዉ የሚጠበቅባቸዉን ግዴታ እንዲወጡ አሳስባለሁ ለራሳቸዉም ጥቅም ሲባል። ከላይ እንደገለጽኩት የህጻናት ትምህርት ቤት በቦምብ ያጋየ ለትግራይ ህዝብ ወደፊት ወዳጂ ይሆናል የሚል እምነት ስለሌለኝ ከህዋአት ዉጭ ማሰብ እንዲችሉ በድጋሚ አሳስባለሁ።
እስከዛዉ በቸር ይግጠመን ሰመረ አለሙ ነኝ ከባህር ማዶ መልካም የፈረንጂ ገና
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments:

Post a Comment