Monday, September 16, 2013

አጤ ምኒልክና ኢጣሊያኖች

“The Study of history is the best medicine for a sick mind!”
Livy 
 የታሪክ ጥናት ለሕሙም አእምሮ ፍቱን መድኃኒት ነው።
በእደ ማርያም እጅጉ ረታ
 ኢትዮጵያ ጥንታውያን ከሚባሉት ሀገሮች አንዷ ስትሆን፣ ከአምስት ሺህ ዓመት ያላነሰ ታሪክ አላት።
በእነዚህ ዘመናት፣ ቀደምት አባቶቻችን ሠርተው፣ ትተውልን ካለፉት ሥራዎች መካከል የአክሱም
ሐውልት፣የላሊበላ ቤተ መቅደስ ሕንፃዎች፣ የጎንደር ቤተ መንግስቶች ለምስክርነት የሚጠቀሱ ናቸው።
ባለፉት በእነዚህ ዘመናት ሀገራችን የእርስ በርስ ጦርነትና ከውጭ በመጡ ወራሪዎች፣ ብዙ ቅርሶች
ወድመዋል፣ የሰዎች ሕይወት ጠፍቷል። ከእዚህ ሁሉ ፈተና በኋላ፣ በዐሥራ ስምንተኛውና ዐሥራ
ዘጠነኛው ምዕት ዓመት፣ ሀገራችን ዘመነ መሳፍንት በመባል የሚታወቀው ጊዜ ውስጥ ገባች። ያ ወቅት
ደግሞ አውሮጳውያን አፍሪቃን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመከፋፋል ወስነው ዘመቻቸውን የጀመሩበት ወቅት
ነበር።
በዚያ ወቅት፣ ይህች በዘመነ መሳፍንት አገዛዝ ኀይሏ የተዳከመችውን ሀገር መልሶ አንድ ለማድረግ፣
የቋራው አንበሳ ካሣ ኀይሉ፣ በኋላ ዳግማዊ ዐጤ ቴዎድሮስ ተብለው የነገሡት ተነሡ። ዐጤ
ቴዎድሮስም በእነዚህ መሳፍንት ላይ በመዝመት ድል አድርገው፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ተመልሳ እንደ
ቀድሞው አንድ እንድትሆን መንገዱን ከፈቱ። ባደረጉትም ዘመቻ፣ አንድም ቀን ድል ሆነው
የማያውቁት ንጉሠ ነገሥት፣ ከአውሮጳውያኑ ጋር በተፈጠረው ችግር፣ የእንግሊዝ ጦር እስረኞቹን
ለማስፈታት በዘመተባቸው ጊዜ፣ እጃቸውን ለወራሪው ጦር መስጠትን እንደ ውርደት ቆጥረውት
መቅደላ አፋፍ ላይ ሽጉጣቸውን ጠጥተው የክብር ሞትን ጽዋ ተቀብለዋል።
ይሁን እንጂ፣ ዐጤ ቴዎድሮስ ከሞቱ በኋላ የተነሡት ነገሥታት እሳቸው የጀመሩትን ዓላማ በመከተል
ኢትዮጵያ ተመልሳ አንድ እንድትሆን አድርገዋል። ከዐጤ ቴዎድሮስ ቀጥለው የነገሡት ዐጤ ዮሐንስ
4ኛ ሲሆኑ፣ በእሳቸው ዘመን የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ እና የጎጃሙ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት


 በዝርዝር ያንብቡ

No comments:

Post a Comment