Thursday, October 31, 2013

ኢትዮጲያኖች እንደንስር! የንስር አሞራ ዳግም ልደት



gn
ንስር አሞራ ከአዋፋት ዘር ለ70 ዓመት የህወት ዘመን መቆየት የሚችል ነዉ። ንስር አሞራ70 አመት እድሜዉን ለመኖር ወይም ለመጠበቅ በ40ኛ አመቱ ላይ ከፍተኘ መስዋትነት የሚጠይቅ ዉሳኔ ይወስናል። የንስር አሞራ የእግር ጥፍር በአግባቡ መስራት የሚችለዉ ለ40 አመት ብቻ ነዉ።
ንስር አሞራ ከተፈለፈለ ጀምሮ 40 ዓመት ከኖረ በዃላ በሰዉነት ክፍሉ ላይ በሚታየዉ ለዉጥ የተነሳ ፤ የአፍ መንቁሩ፤የእግሩ ጥፍር ና ላባዉ እንደበፊቱ ሊያገለግሉት አይችሉም። የእግሩ ጥፍሩ ደካማ በመሆን አደኑን አይዝለትም ፤ረጅምና ስል መንቁሩ ይታጠፋል ፤ ላባዉ በሰዉነቱ ይለጠፍና ክብደት ስለሚፈጥር ፤እንደልቡ አይበርም ። በዚህ ወቅት ንስር አሞራ ፡ በሁለት ዉሳኔዎች ላይ ይወድቃል ፤ ዝምብሎ በመቀመጥ ሞቱን መጠበቅ ወይም 5 ወር የሚፈጅ ስቃይና መከራ ያለበት መሰዋትነትን በመክፈል ቀሪ 30 አመቱን እንደ ወጣት ንስር መኖር።
ሰላሳ ተጨማሪ ዓመት ለመኖር የአምስት ወር መሰዋትነት መክፈል፤
ንስር አሞራ ቀሪ 30 ዓመቱን ለመቀጠል ከፍተኛ ተራራላይ በመዉጣት ጎጆ ይቀልሳል።ንስር በተራራዉ ላይ ጎጆ ከቀለሰ በዃላ የመጀመርያ ስራዉ የአፉን መንቁር ከአለት ጋር በመፋቅ ነቅሎ መጣል ነዉ ይህም ከፍተኛ ህመምና ስቃይ አለዉ ይሁን እንጂ አዲስ መንቁር ለማዉጣት ይህንን ማድረግ የግድ ነዉ ፤ ከዚያም አዲስ መንቁር ከወጣላት ወይም ከበቀለለት በዃላ በአዲሱ መንቁር የእግሩን አሮጌ ጥፍር ነቅሎ ይጥለዋል ። አዲሱ የእግር ጥፍር ከበቀለለት በዃላ ይህንን አዲስ ጥፍር እንደመሳርያ በመጠቀም በሰዉነቱ የተጣበቀዉን ጥቅጥቅ ያለዉን ላባ ነቃቅሎ ጥሎ አዲስ ላባ እንዲበቅል ያደርጋል። ይህ ህመምና መከራ ያለዉ ድርጊት ነዉ ። ከዚያም የ 5 ወር የማገገሚያ ጊዜ ካጠነቃቀቀ በዃላ እንደገና ራስን የመዉለድ የትግል ሂደት ይጠናቀቅና ፡ተጨማሪ 30 ዓመቱን በሰማይ ላይ እየበረረ ና እያደነ በደስታ ይኖራል።
እኛ ኢትዮጲያኖች እንደንስሩ መሆን ያቅተን ይሆን?
በህወታችን ዉስጥ የምንፈልጋቸዉ ለዉጦች አንዳንድ ግዜ በአስቸጋሪና መራራ ሁኔታዎች ዉስጥ እንድናልፍ ግድ ይሉናል የሰዉ ልጅ በህይወቱ መከራ ሲገጥመዉ ከዚህ አስቸጋሪ ህወት ለመዉጣትና ለመለወጥ ፤ ብሎም ደስተኛ ለመሆን የህይወት ልምዱን መለወጥ ፤አሮጌ ልምዱን ፤ትዝታዎቹን፤ የእለት ተእለት ኑሮዉን አሽቀንጥሮ መጣል ግድ ይለዋል ፤ እነዚህ አሽቀንጥረን የምንጥላቸዉ ነገሮች ግን ለማስወገድ ከፍተኛ መሰዋትነት ይጠበቅብናል ፤ ይህንን መስዋትነት ከከፈልን ልክ እንደንስር አሞራዉ ቀሪህወታችንን በደስታ ልንኖር እንችላለን።
እኛ ኢትዮጲያኖች በአሁን ጊዜ ከመቸዉም ጊዜና ዘመን በከፋ መልኩ በሀገራችንም ሆነ በስደት ተሰቃይተን ተዋርደን የምንኖርበት ዘመን ሆኖ ሳለ ረዥሙን ዘመናችንን ለመኖር ትንሽ መሰዋትነት በመክፈል አሮጌ ልምዳችንንና ትዝታዎቻችንን፤አሽቀንጥሮ መጣል ተቸግረን ፤ የራሳችንን ቀሪ ህወት ብቻ ሳይሆን የዚችህን ለዘመናት በደም መሰዋትነት የኖረች ሀገር እድሜ ለማስቀጠል ፤ተስማምቶና ተባብሮ መስራት አቅቶን ፤ሀገራችን እላይዋላይ በተጣበቁ መዥገሮች ወዳለመኖር እየወረደች እያየን ፤ዝምብለን እንገኛለን አልያም ባላስፈላጊ ነገሮች ላይ አተካሮ ይዘን በአሮጌ ልምዶቻችን ተተብትበን እንገኛለን።
በኢትዮጲያ ታሪክ ዉስጥ በየዘመኑ የነበሩ ገዢዎች ጊዜያቸዉን ጨርሰዉ ሲወገዱ/ሲሄዱ/ አንጻራዊ ጠንካራ ወይም ደካማ ኢትዮጲያን ትተዉ ነዉ የሚሄዱት፤ወይም ኢትዮጲያ የምትባል ሀገር አትጠፋም።አሁን ኢትዮጲያ ባለችበት ሁኔታ የምትቀጥል ከሆነ ይህ ይኖራል ወይስ ይቀጥላል? በፍጹም። የወያኔ አገዛዝ በዚህ ከቀጠለ ወይም ጊዜ በጨመረ ቁጥር ተገዶም ሆነ በራሱ ጊዜም ቢሄድ ኢትዮጲያ የምትባል ሀገር ልናገኛት አንችልም ወይም አሁን ያለዉን የኢትዮጲያ ግዛት ማግኘት ዘበት ነዉ የሚሆነዉ።ምክንያቱም የገዥዉ አካል ኢትዮጲያን የማጥፋትና የማፍረስ እቅድ ይዞ የተነሳና ለዚሁም ሀያአራት ሰአት የሚሰራ ሲሆን በአንጻሩ ያለንዉ ደግሞ ፤ኢትዮጲያ ኢትዮጲያ ከማለት ዉጭ መሬት የወረደ ስራ መስራት አቅቶን ሃያሁለት አመት አስቆጥረን በተቃራኒዉ ለጥፋቱ ሃይል ምቹ ሆነናል።
እንደሀገር ካሰብን ጊዜዉ አሁንም አልረፈደም እንደ ንስሩ ከፍ ያለ ተራራላይ እንዉጣ ዝቅ አንበል ከፍባልን ቁጥር ጥሩ እይታ ይኖረናል ጥሩ እይታ ታጋሽ፣አስተዋይ ፣ቻይ ያደርገናል፤ከዛ በዃላ አሮጌ አስተሳሰባችንን ፣የማያስማሙንን፣ እኔ ብቻ የሚለዉን ስሜታችንን ፣የሚያለያዩንን፣ መንቁራችንን ፣ጥፍራችንን ወደዚያ ነቅለን ጥለን ፤ በሚያስማሙንን ፣በሚያቻችሉን ፣እንተካቸዉ። ይህንን ስናደርግ ወያኔን ታሪክ አድርገን ኢትዬጲያን እንታደጋታለን።
ሞት ለወያኔ !
ትንሳኤ ለኢትዮጲያ !
Amha Alemu
Norway
ይገባናል – we deserve !

zehabesha

No comments:

Post a Comment