Wednesday, October 30, 2013

አወጋን “ለጉልበት ሥራ ወደ ሁመራ የሚሄዱ የአማራ ተወላጆች ኩላሊት ለሱዳኖች እየተሸጠ ነው” አለ


(ዘ-ሐበሻ) ለጉልበት ሥራ ወደ ሁመራ የሚሄዱ የአማራ ተወላጆች ኩላሊት ለሱዳንኞች እየተሸጠ ነው ሲል አወጋን (የአማራ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ) ለዘ-ሐበሻ በላከው መረጃ አመለከተ። ንቅናቄው በላከው መረጃ “ከደቡብ ጎንደር፣ ከምዕራብ እና ምስራቅ ጎጃም፣ ከሴሜን ወሎ ለጉልበት ሥራ ወደ ሁመራ የሚመጡ ወገኖቻችን ባሰሪዎቻቸው አና ባካባቢው በዚህ ሥራ በተሰማሩ (የትግራይ ተወላጆች) ግፍ እየተሰራባቸው ነው” ሲል ከሷል።
(ሁመራ ከተማ)
(ሁመራ ከተማ)

“ባለፉት 2 ወራት ብቻ የ16 ሰዎች አስከሬን በተለያየ አካባቢ ወድቆ የተገኘ ሲሆን ጎዳዩን ቀለል በማድረግ እና እውነቱን ሰው እንዳይገነዘብ ሲባል የተለያዩ መላምቶች በመንግስት ሆን ተብሎ ተሰጦታል” ያለው የአወጋን መረጃ “ለምሳሌ በአንድ ሳምንት ዉስጥ በተደጋጋሚ የተፈፀመውን ይሄን ድርጊት በቀጥታ በብሔሮች መካከል በተነሳ ግጭህት (የወሎ እና የጎጃም በሚል) እርስ በርስ በጩቤ እየተዋጉ ነው በማለት ጉዳዩን አድበስብሶት የቀረ ሲሆን ሌሎች ገለልተኛ ሚዲያዎችም እሄንኑ በማስተጋባት እውነቱ ተደብቆ ወንጀሉ ግን ቀጥሏል::” ብሏል።
በሁመራ ከተማ ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ የህገወጥ መሳሪያ ዝውውር በስፋት የሚፈፀም መሆኑን ያጋለጠው የአወጋን መረጃ በዚህ ሥራ የተሰማሩት ሁሉም የትግራይ ተወላጆች ከሱዳኖች ለሚቀበሉት መሳሪያ ክፍያ እንዲሆን የሚሰጠው የገበሬዎችን ኩላሊት ነው ይላል። “እንዲህ አይነት ሥራ በሱዳን በኩል ወደ እስራኤል በህገወጥ መልኩ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ወገኖቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለ እንደሆነና አልፎ አልፎም በሱዳን በገድሃሪፍ እና አጎራባች አካባቢዎች ድረስ በመምጣት ካምፕ ዉስጥ በመግባት ኢትዮጵያውያኑን ስደተኞች አፍኖ በመያዝ ብዙ ሺ ዶላር በማስከፈል ይለቋቸዋል መክፈል ያልቻሉትን ግን ኩላሊታቸውን በማውጣት ለእልፈተሞት ይዳረጋሉ::” በማለት አወጋን ለወገኖቻችን እንድረስላቸው ሲል ጥሪውን ከሰሜን ጎንደር አስተላልፏል።
ለአወጋንን ክስ የመንግስት አካላትን ምላሽ ለማካተት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

zehabesha

No comments:

Post a Comment