Tuesday, August 20, 2013

በኔቫዳ የሚገኘው ኤርያ 51 እውነት መሆኑ ተገለጸ CIA ‘Area 51′ exists

እውነቱ በትክክል ተገኝቷል!! የተለዩ አለማት ፍጡራን ማዕከልና የምርምር ጣቢያ ነው የሚባለው ይህ ኔቫዳ ሰቴት ይገኛል ይባል የነበረው እና ለብዙ አመታት ተደብቆ የነበረው አካባቢ 51(Area 51) እውነት መሆኑ በዪናይትድ ስቴትስ መንግስት ምስክርነት ተረጋገጠ፡፡ አካባቢ 51(Area 51) የተለያዩ አለማት ፍጡራን ቀዶ መመራመሪያ ፣ በድብቅ የሚስጥረኞች መሰብሰቢያ ይባል የነበረው ትክክል እንዳልነበርና ቦታው በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት በሚስጥር ዩ – 2(U – 2) የሚባሉ የስለላ አውሮፕላኖች ማምረቻ እንደነበር ተገልጿል፡፡
እውነታው የተረጋገጠው በነጻነት የመረጃ ጥያቄ መሰረት በጆርጅ ታውን የኒቨርሲቲ አማካኝነት ነው፡፡ በዚህም መረጃ መሰረት ምንም የተለያዩ አለማት ፍጡራን( UFOs) የሚባሉ እንደሌሉና የተደረደሩ አውሮፐላኖች ብቻ እንዳሉ መረጃው ያትታል፡፡ ቦታውም ኔቫዳ ውስጥ ገሩም ሶልት ሌክ አካባቢ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
የተባለው ነገር እውነት ከሆነ በ Area 51 ላይ ይደረግ ነበር የተባለው የተለያዩ አለማት ፍጡራን ቀዶ መመራመርና በ1947 ዓ.ም. ኒው ሜክሲኮ ውስጥ ወደቀ የተባለው የተለዩ አለማት ፍጡራን መንኮራኩር እውነት ሊሆን እንደሚችል ይገመታል፡፡
እንደሚባለው ከሆነ ኒው ሜክሲኮ የወደቀው መንኮራኩር ወደ Area 51 ተወስዶ ለምርምር እንደቀረበና ሳይንቲስቶችም በድብቅ ከነዚሁ የተለዩ አለማት ፍጡራን ጋር ስብሰባ ያደርጉ እንደነበር ተነግሯል፡፡ ሌሎች የ Area 51 ስራዎች እሚባሉትም የአየር ንብረት ቁጥጥር ፣ ድብቅ የጦር መሳሪያ ምርትና ቴሎፖርቴሽን እንደነበሩ ሌሎች ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን መረጃዎች እንደሚሉት ቦታው በ1955 ዓ.ም. ባቶሚክ ሀይል ኮሚሽን የተገኘና ከዚያ በኋላ ለዩ – 2 አውሮፕላን ፓይለቶች ማሰልጠኛ እንደተሰጠ ተገልጿል፡፡ ቦታውም በዩኤስ አሳሾች በ1955 ዓ.ም. ለዚህ የህቡእ ሀይል ማመንጫነት የተመረጠ እነደሆነና ፐሬዝዳንት አይዘንሀወር የዚህን መሬት ግዥ እንደፈቀዱት ተገልጿል፡፡ ቀጠሎም ሲ.አይ. ኤ በ1957 መቦታውን ሲለቀው የዩ. ኤስ አየር ሀይል ለየ – 2 ፓይለቶች ማሰልጠኛ እንደተረከበው ዘገባው ይናገራል፡፡ አውሮፕላኖችም በረጅም ከፍታ በመብረር ለአየር መቆጣጠሪያና ትንበያ ስለላ ወደ ሶቪየት ዩኒየን ፣ ቻይና ፣ ሰሜን ቪየትናምና ኪውባ በ1950ዎች፣ 60ዎችና 70ዎች ለሶስት አስርት አመታት ይላኩ ነበር ፡፡
ካርታው እንደሚያሳየው ቦታው የሚገኘው በአንድ ወቅት የመአድን ማውጫ የነበረ ቦታ ጎን የተከለከለ የአየር መረፊያ ላይ እንደሆነ የጆርጅ ታውን የኒቨርሲቲ ሪፖረት ገልጿል ፡፡
ጀፍሪ ሪቸልሰን በብሄራዊ የሚስጥር ሰነድ እንደገለጹት የ Area 51 ሚስጥርነት አልቆ ስለስራው አዲስ የመረጃዎች ገለጻ መጀመሪያ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡
By Sodere Team

No comments:

Post a Comment