Friday, August 30, 2013

ጓደኛውን በገጀራ ቆራርጦ የጣለው ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ነው

በተስፋሁን ብርሃኑ
ፖሊስና ርምጃው
‹‹እኔ ስራ አስገብቼው ሳለ ለአለቃዬ ዘወትር ስለ እኔ መጥፎ ነገር ይናገራል ያለውን ጓደኛውን ሶስት ቦታ ቆራርጦ የጣለው በፍርድ ቤት ጉዳዩ እየታየ ነው፡፡
ተጠርጣሪ ሀጎስ ገብሩና ሟች አምሳሉ ምትኩ በአራዳ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 11/12 ልዩ ቦታው አራት ኪሎ ዩንቨርሳል ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ውስጥ በጥበቃ ስራ ላይ ተሰማርተው ይገኙ ነበር፡፡ ተጠርጣሪው ‹‹ዋና ፀባችን ነው ያለው እኔ ስራ አስገብቼው ልወደድ በማለት ዘወትር ስለ እኔ መጥፎ ነገር መናገርና እያመሸ እየመጣ ስራ ተበድሏል በማለት ያጣላኝ ነበር›› ብሏል፡፡ በምርመራ ወቅት፡፡ ይሄኔ ቂም የያዘው ተጠርጣሪ ሀጎስ ገብሩ ከሁለት ወር በፊት ለግድያ መዘጋጀት ይጀምራል፡፡
ለግድያ የሚያስፈልገውንም ከብረት የተሰራ ገጀራ ከመርካቶ እንደገዛ ተናግሯል፡፡ ሟች አምሳሉ ሲመጣ ‹‹እባክህ ራት በልቼ ልምጣ ስለው ባትበላ ምን አገባኝ አፈር ብላ ብሎኝ ወጣ›› ይላል ተጠርጣሪው በምርመራ ወቅት፡፡ ሟች በዚሁ ቀን አምሽቶ ሲመጣ በደሉ በዛብኝ ያለው ተጠርጣሪ በሩን ከከፈተለት በኋላ ሟችን በሩን እንዲዘጋው ከነገረው በኋላ ፊቱን ወደ በሩ ሲያዞር በያዘው ገጀራ ፊቱን ይመታዋል፡፡ ከዚያም ከመሬት ከወደቀ በኋላ አንገቱ አካባቢ ሲመታው ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉ ተገልጿል፡፡
ተጠርጣሪው የሟችን አስክሬን ውሃ ወዳለበት ቦታ በመውሰድ በገጀራው ወገቡንና ሁለት እግሮቹን ቆራርጧል፡፡ ከወገብ በላይ አራት ኪሎ አካባቢ በሚገኝ ድልድይ መሻገሪያ ውስጥ የጣለው ሲሆን ግራና የቀኝ እግሩን ደግሞ በቢጫ ኩርቱ ፌስታል ጠቅልሎ የሚሰሩበት አካባቢና ብርሐንና ሰላም ማተሚያ ቤት ከፍ ብሎ በሚገኘው ሳጠራ ጠጅ ቤት አካባቢ ሊጥለው ችሏል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ የሰው መግደል ወንጀል መርማሪ ቡድን ወንጀሉ በተፈፀመ ሰሞን ከህብረተሰቡ ጋር በተደረገ ቅንጅት ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ሊያውሉት ችለዋል፡፡ መርማሪ ግሩም ታረቀኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ የግድያ ወንጀል መርማሪ አስፈላጊውን የሰውና የሰነድ ማሰረጃ አሰባሰበው ካጠናቀቁ በኋላ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት መዝገቡን ልከው ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡
freedom4ethiopian

No comments:

Post a Comment