Saturday, August 31, 2013

የሀገር ውስጥ የደህንነት መምሪያ ሃላፊ በቁጥጥር ስር ዋሉ

የሃገር ውስጥ የደህንነት መምሪያ ሃላፊው አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥር ስር ዋሉ።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋሉት የነበራቸውን ስልጣን ያለ አባብ መጠቀም  ምንጩ ያልታወቀ ሃብት በማፍራት የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል በሚል  ተጠርጥረው ነው
ከፌደራል ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን የተገኘው መረጃ እንደሚያስረዳው  ተጠርጣሪው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል።
ኮሚሽኑ ግለሰቡ ፈጽመውታል ከተባሉ የሙስና ተግባራት ጋር በተያያዘ ሌሎች ተያያዥ ምርመራዎችን እያካሄደ ይገኛል።
የዛሬ አመት ገደማ ኮሚሽኑ በአቶ ወልደስላሴ  ወንበር ላይ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩ አቶ አይቼው ተፈታን በተመሳሳይ ወንጀል ከሷቸው በአሁን ጊዜ  ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ነው  
አቶ አይቼው ከገቢ በላይ ምንጩ ያልታቀ ሃብት አፍርተዋል የተባሉባቸው ሆቴሎች እና ሌሎች ንብረቶች በአሁን ጊዜ መታገዳቸው ይታወቃል።


ምንጭ ፡-(ኤፍ)

No comments:

Post a Comment