Thursday, August 15, 2013

ምስራቅ ሐረርጌ በርካታ ሰዎችን በመንከሱ እንዲገደል የተፈረደበት ዝንጀሮ ተይዞ የፍርድ ውሳኔው ተፈፀመበት

ምስራቅ ሐረርጌ በርካታ ሰዎችን በመንከሱ እንዲገደል የተፈረደበት ዝንጀሮ ተይዞ የፍርድ ውሳኔው ተፈፀመበት Baboon in Ethiopia sentenced to be killed

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 7 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ ቀበሌ 01 20 ሠዎችን ነክሶ ጉዳት አድርሷል የተባለው ዝንጀሮ በሞት እንዲቀጣ ፍርድ ቤት እንደወሰነበት ይታወሳል ።
በወቅቱ ዘገባችን ላይ እንደተመለከተውም የቀበሌው ነዋሪ የሆኑት አቶ ደቻሳ አብዲ አብራሽ በ19997 ዓ.ም ጀምሮ ዝንጀሮውን አሳድገውታል ።
ዝንጀሮው የ7 ዓመት ከ7 ወር ዕድሜ እስኪደርስ ከቤት እንሰሳም ጋር ሆነ ከሰው ጋር ሰላማዊ ህይወትን ይኖር ነበር።
ከግዜ በኋላ ግን ባህሪው ተለወጧል።
የባህሪው ለውጥ አመላካች የሆነው ሰዎችን መተናኮልና መናከስ መጀመሩ ነው ፤ በመሆኑም ዝንጀሮውን ማሰር በባለቤቶቹ የተወሰደ እርምጃ ነበር።
መታሰሩን ያልፈቀደው ዝንጀሮው የታሰረበትን በመበጠስ ሰተት ብሎ ወደ ጨለንቆ ከተማ ይገባል።
በከተማዋ እየተዘዋወረም 20 ሰዎችን በመንከስ ጉዳት ያደርስባቸዋል።
ከዚህ በኋላ የሜታ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ዝንጀሮውን በጣቢያው ያስረዋል።
ነገር ግን ሐምሌ 21 ቀን 2005 ከፖሊስ ጣቢያው የታሰረበትን ገመድ በጥሶ በመውጣቱ ምክንያት የወረዳው ፖሊስ ዝንገሮውን ለመያዝ የፖሊስ አባላትን ያሰማራል።
የከተማዋ ነዋሪዎች ግን ባሳለፍነው ሰኞ በፍርድ ቤት በመሰባሰብ አቤት ይላሉ።
ፍርድ ቤቱም የነዋሪውን ስጋት ከግምት በማስገባት ዝንጀሮው በተገኘበት ይገደል ሲል ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ፖሊስም የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ለመፈፀም ዝንጀሮውን በማደን ላይ የነበረ ሲሆን ፥ የምስራቅ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህህዝብ ግኑኝነት ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር ስዩም ደገፉ እንደተናገሩት ዝንጀሮው ከትናንት በስቲያ በቁጥጥር ስር ውሎ የፍርድ ውሳኔው ተፈፅሞበታል።

No comments:

Post a Comment