የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ቃሲም ፊጤ በቁጥጥር ስር ዋሉ
ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው
አቶ ቃሲም የተጠረጠሩበትን የሙስና ወንጀል መሠረት በማድረግ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ኮሚሽኑ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
ቀደም ብሎ ጥያቄ አቅርቧል፡፡
ምክር ቤቱም የግለሰቡ
ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ የቀረበለትን የሰነድና የውሳኔ ሐሳብ ከመረመረና የአሠራር ሒደቶችን ግንዛቤ ውስጥ ካስገባ በኃላ ሰኔ
28/2005 ያለመከሰስ መብታቸውን ያነሳ መሆኑንም መግለጫው አመልክቷል፡፡
የተጠርጣሪው ያለመከሰስ
መብት እንዲነሳ ምክር ቤቱ የደረሰበትን ውሳኔ ተከትሎ ኮሚሽኑ አቶ ቃሲምን በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሲሆን ፥ የተጠርጣሪነት ቃላቸውን
በመቀበል አስፈላጊው ሕጋዊ ሥራ ማከናወኑንም ነው ያመለከተው ፡፡
ተጠርጣሪው ከዚህ
ቀደም ከሀገር ወጥተዋል በሚል ሲወራ
እንደነበር የሚታወስ ቢሆንም ፥ ዛሬ ማምሻውን በቁጥጥር ስር የዋሉት በቢሯቸው
እንዳሉ መሆኑን ነው ኮሚሽኑ ያስታወቀው ።
ግለሰቡ ቀደም ብለው ከሀገር የወጡትም ለስልጠና እንደነበር ነው የተመለከተው ።
ነገ በፌደራሉ ከፍተኛ
ፍርድ ቤትም ቀርበው ቀጠሮ ይጠየቅባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል
።
source....fababc.com
No comments:
Post a Comment