Thursday, November 28, 2013

ሕገ ወጥ ስደተኛ (illegal immigrant)

ሕገ ወጥ ስደተኛ (illegal immigrant)

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
An Ethiopian worker argues with Saudi security forces while waiting for repatriation in Manfouha
ምን ማለት ነው እሱ ወዳጀ፤ ይሄ ሕገ ወጥ ስደተኛ
ወዶ የሚሰደድ ከሌለ፤ ከሀገሩ የሚርቅ መከረኛ
ነፍሱን ለማትረፍ የሻ ሰው፤ ይሸሻል እንጅ ባመራው
እንግዳ አይደለ ወይ ጎብኚ፤ ፈቃድ ጠይቆ የሚገባው
እስኪ ንገረኝ እባክህ፤ ለእናንተው መሐመድ ሰዎች
ተቸግረው ለተሰደዱት፤ ከሀገራቸው ላለመሆን ሟች
ቪዛ ተመቶላቸው ነበረ? ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ?
   አሳልፋቹህ ስጡን ብለው፤ በጠላት ለሰይፍ ሲታሰቡ
   ውሰዷቸው ተብለው ነበር? ወይስ ቤዛ ሆነ እርግቡ?
   ውጡልን ተብለውስ ነበር? ፊቱን ነስቷቸው ሕዝቡ?
   አንተ ግን ውለታ ቢሱ፤ አምላክ የማታውቅ የማትፈራ
   የነፍስ ብለው የተጠጉትን፤ ለማምለጥ ከአጋንንት ጭፍራ
   እያረድክ ፈነገልካቸው፤ ደፍረህ አርክሰህ በጠራራ
   ይሄ ነው ላንተ ጽድቅ ማለት፤ ደም ጠጥቶ መስከር ግፍ ሥራ
ከሰይፍህ የተረፉትን፤ ደክሞህ ሰልችቶህ መተራ
እያነክ አስረከብካቸው፤ ለግዞት ሞት ለመከራ
አምላክን የፈራ ማለት፤ ለሰብአዊነትም ያደረ
ምርጫ ያጣን መርዳት እንጅ፤ ድጋፍን መስጠት ለተቸገረ
ያለውን መቀበል አይደለም፤ ለሥጋዊ ጥቅም እየመከረ
በሥጋ ገበያው ገብቶ፤ ካዝና የሚሞላን እየጨመረ

goolgule

No comments:

Post a Comment