Wednesday, November 27, 2013

ኧረ እነማን ናቸው? (ጌታቸው ቃሉ)

ኧረ እነማን ናቸው? (ጌታቸው ቃሉ)


ጌታቸው ቃሉ
ከየት ነው የመጡ ከነጥላቻቸው?
የሀገር መሪ ሆነው ሕዝብን መጥላታቸው
ምንድነው ዓላማው? ወንበር መያዛቸው
እንቅልፍ ሳይተኙ እንዲ መኖራቸው
ሀገር አይበድልም ምን አስቀይሟቸው?

ሕዝብን ከሕዝብጋ ሊያጣሉ ሴራቸው
ኧረ ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ናቸው?!
ሠራዊቱስ ምነው እንዲ አከበራቸው?
ከእናት ካባቱ እውን በልጦባቸው
እህቶቹን ሁሉ ገረድ ላረጋቸው
ወንድሞቹን አስሮ ጭራሽ ደፍረዋቸው
ሀገሩን ቆራርሰው ለባዳ ሸጧቸው
ኧረ በምን ሂሳብ ዘብ የቆመላቸው?!
ሰምተን የማናቀው ጉድ ተፈፀመብን
መራዝ፣ መራባችን መጠማቱን ትተን
እንዴት ባገራችን ክብር እናጣለን?!
ምን ሆኗል ትውልዱ? በቁም የሞተበት
ለክብሩም ለሆዱ እንዲ ያላወቀበት
እነሱ ሲበሉ ዐይቶ ያፋሸከበት
ዕንፃ ሲገነቡ ድንጋይ ያቀበለበት
ምን ዓይነት ምታት ነው ለሱስ ያረጉበት
ፍፁም አይመስለኝም ሀገሬ የቆመች
በሰመመን ዕንቅልፍ እንጂ የወደቀች
ማን ፈቅዶ ይገፋል ከመብቱ
አደለም ለመብላት ለወሬም ከመቱ
የዓላማ ሳይሆን ጥላቻ መሆኑን
የሚያስጨንቃቸው ባንዳነታቸውን
አውቀን ካልተነሳን አይ ካላልናቸው
እነዚህ ጭራቆች ያወቁ መስሏቸው
ሀገሩን ለማጥፋት የቆረጡ ናቸው።
ጌታቸው ቃሉ

ethiopiazare

No comments:

Post a Comment