Friday, November 29, 2013

የሚኒሶታዉ ደብረ ሰላም መድሃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወያኔ እጅ መንሻ አይሆንም


ከወንድሙ በላይነህ (ሚኒሶታ)
ሰሞኑን ከማቀርባት እህቴ ጋራ ጨዋታ ጀምረን ሳዉዲ አረቢ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ሥላለዉ ስቃይና መከራ ስናወራ እህቴ ቆጣ ብላ፦ አይ እኛ ስለነሱ መከራ ልባችን እዬደማ ተጨናንቀናል፤ ሌሎች በቤተክርስቲያናችን ላይ ከሚዶልቱ ሰይጣኖች ጋር ዛሬ ተጋጭቸ መጣሁ አለችኝ፦ የምን ግጭት ስላት አባወች እኮ ቤተክርሲቲያን ወዳገርቤት ሲኖዶስ አስተዳደር ኢንዲገባ ቅስቀሳ አድርጊ ብለዉኝ በጣም ተናደድኩ ብላ ስትነግረኝ ከርሷ በባሰ ድንጋጤዉ እኔንም በቁሜ አፈዘዘኝ። ኢትዮጵያዉያን ባዓለማት ተበትነዉ እያለቀሱ፦ በአገራቸዉ መኖሪያ አተዉ በሰዉ አገር እየተደበደቡ፦ እዬተደፈሩ፦ እየሞቱ እንዴት ዛሬ ወደወያኔ ለመግባት ቅስቀሳ አካህጅ ይሉኛል ብላ አለቀሰች። ጀሮ ከተማ ነዉ ሁሉ ይሰማበታል፦ በእርግጥም ከሃያ ሶስት የግፍ ስርዓት ዓመታት በሗላ ይህንን መስማት ያስደነግጣል፦ እንዲያዉም በዉጭ ያለን ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በሳዉዲ አረቢያ እዬተጎዱ ላሉ ወገኖቻችን ተባብረን በአንድ ላይ በምናለቅስበት ሰዓት ይህን አፍራሽ ስራ ከጀመሩ መድሃኒዓለም ስራዉን ይሰራል አልኳት እና ጨዋታየን አቋረጥኩ። deb
ደሙ የዋጀበትን መስቀል ተሸክመዉ ግን የዕምነት ይህይዎታቸዉ በመዋዕለ ንዋይ ህሊናቸዉ የተሰዎረ የወያኔ ምልምል ቄሶችና ዘማሪዎች ለጥቅማቸዉና ለወደፊት ሹመታቸዉ የባዘኑ ተስፈኞች ቤተ ክርስቲያናችን ለወያነዉ ፓትራሪክ ለማስረከብ ሃያ አራት ሰዓት በሴራ ተጠምደዉ ደፋ ቀና በማለት ላይ ይገኛሉ። እኩይ ስራቸዉን ተግባራዊ ለማድረግም በመድሃኒአለም በራፍ የታየ ምዕመናንን ሁሉ በጌቤታቸዉ እዬጋበዙ ወደ አገርቤቱ ሲነዶስ ለማስገባት ቀስቅሱ እያሉ መሃላ የሚያስገቡት ቁጥር ጥቂት አይደሉም። በወያኔ ዉስጣዊ ሎሌነት ታማኝ የሁኑት ቀንደኛወች ከአሁኑ ጀምሮ የሚቸራቸዉ (የሚሰጣቸዉ),ሹመት ምን እንደሆነ፦ በኢትዮጵያ ዉስጥ የከፈቱት ቢዝነስ ለነሱ ብቻ ሳይሆን ለአገሪቱ ተስፋ እንደሚሆን ተረጋግጦላቸዉ፦ ተማሪ የሆኑ ዘማሪያን ም ለ SCHOLAR እንደሚከፈላቸዉ ቃል እዬተገባ መሆኑ አንዳዶችን ነገሩ አስደንግጧቸዉ ለመቃወም በመነሳሳት ላይ ናቸዉ።
የሚገርመዉ ነገር አብዛኛወቹ በቤተ ክርስቲያኑ ምስረታና ግንባታ ያልነበሩ፦ እዳ ከተከፈለ ለስዉር ዓላማ በወያኔ የዘር መስመር አምነዉ ለመጥፎ ተግባር የተሰገሰጉ፤ ነገር ግን እራሳቸዉን መስራች ነን ብለዉ የመዘገቡ፦ በድምጽ ለማሸነፍ የአብዛኛ አባላት ድጋፍ ለማግኘት በየሰፈሩ እየተዘዋወሩ መልካም ዘመድ መስለዉ ለማሳመን የቆጡን የባጡን እያሉ ነዉ። ለመሆኑ ወያኔ ምን አዲስ ነገር ይዟል ብለዉ ሊያሳምኑን ፈለጉ? የህዝቦቻችን ድምጽ ለሃያ ሶስት ዓመታት በወያኔ ሙሉ በሙሉ ታፍኖ፤ ሃይማኖታችን በዘር ስርዓት ተቦርቡሩ፤ በወያኔ የበላይነት በየአድባራቱ ተመዝብሮl፦ የዕምነት ነጻነት ተነፍጎ። አሁን በያዝነዉ ወር እንkኳን በሳዉዲ አረቢያ ጥቃት ለደረሰባቸዉ ኢትዮጵያዊያን በአዲሳበባ ድምጻቸዉን እንዳያሰሙ ወገኖቻችን ተከልክለዉ መንግስት አጣን እያሉ ከሰባት ወራት ጩኸት በሗላ ለሞት ሲዳረጉ፦ አገራዊ ዉርደት ሲደርስብን እንዴትስ የወያኔ አጋርነት አሁን ይሞከራል? ወይስ አባ ማትያስ የወያኔ የዘር ምልምል ካድሬ ጳጳስ አደሉም ብለዉ ለማሳመን እየተጃጃሉ ነዉ። እኛማ አዉቀናል……:አያጅቦ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ።
በሚኒሶታ ኢትዮጵያዉያን በህይወት እያለን ደብረ ሰላም መድሃኒአልምን ወያኔ አይረከበዉም። አወ ሰሞኑን እኛን እዉነተኛ አማኞችን ለማዋረድና በወያኔ ቃል የተገባዉን ለማሳካት፤ ግድያ ለመጣል፤ የነጻነቱን ትግል እንደበረዶ ለማቀዝቀዝ፦ በአህዝበ ክርስቲያን ላይ የመርዝ ሴራ የምትረጩ ሁሉ መድሃኒአለም በሩን ዘግቷል። ከወደቃችሁ በሗላ ወያኔ እንደማያነሳችሁ ካሁኑ እወቁት፤የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች እንዳይሆንባችሁ ወዮላችሁ። ይልቅስ እናተዉ የሃጣን ሎሌ ሁናችሁ ንጹ ጻድቃንን ግራ አታጋቡ፤ሰላም አታችሁ ህዝበ ክርስቲያን አታስቆጡ። እዉነት ልበላችሁ እሚመቻችሁ ከሆነ ከዚህ አሜሪካ ካሉ የወያኔ ቤተክርስቲያናት መጀመሪ ጠቅላችሁ ግቡና የወያኔን አስተዳደር ሞክሩት በቤተ ክርስቲያን እንኳ ምርጫ ማካሄድም አትችሉም። እኛ የምንለዉ መድሃኒአለምን ተዉት ወይም ሃብታችሁን ይዛችሁ ልቀቁት። ከእንግዲህ ይህ የተቀደሰ ቦታ የንግድም ሆነ የስልጣን ቦታም አይሆንም። እናንተ እጃችሁን ስጡ የዕምነት ቦታችን ግን እጅ መንሻ ለማድረግ ፍጹም አትሞክሩ። ህዝበ ክርስቲያን ሆይ የእግዚአብሔር ቤትህን ጠብቅ።
ከወንድሙ በላይነህ
ወስብሃት ለእግዚአብሔር
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments:

Post a Comment