Friday, July 26, 2013

በሙስና የተጠረጠሩት የደብረ ጽጌ ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ

በሙስና የተጠረጠሩት የደብረ ጽጌ ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ

ሐራ ተዋሕዶ ብሎግ እንደዘገበው፦
በተጭበረበረ ውል ደብሩን ከ3 ሚልዮን ብር በላይ በማሳጣትና ሰነድ በማሸሽ ይጠየቃሉ
ከጥቂት የሙዳይ ምጽዋት ገቢ ምርመራ ብቻ ከ2 ሚልዮን ብር በላይ ጉድለት ተገኝቷል
የአብዛኛዎቹ የደብሩ ሕንጻ ሱቆች የኪራይ ውል በትክክለኛ ሰነድ የተፈጸመ አይደለም
ለማተሚያ ቤት አገልግሎት በተከራየው ክፍል በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የማይታወቅ ሞዴላሞዴል
እንደሚታተምበት ተጠቁሟል
የፕሮቴስታንት ቤተ ጸሎት እንደሚያዘወትሩ የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል
በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ
ዲያቆን ምሩፅ ትኵዕ በተጭበረበረ ሰነድ ከተፈጸመ የኪራይ ውልእና ለሒሳብ
ምርመራ የሚፈለጉ የሙዳይ ምጽዋት የገንዘብ ቆጠራ ቃለ ጉባኤዎችን
ከማሸሽ የሙስና ወንጀል ጋራ በተያያዘ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው
ተገለጸ፡፡
ዋና ጸሐፊው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ ሐምሌ ፲፪
ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ረፋድ ላይ በደብሩ ጽ/ቤት ባሉበት ሲኾን ከዋና ጸሐፊው ጋራ
በተጭበረበረው የኪራይ ሰነድና ውል ለደብሩ የሚገባውን ክፍያ ሳይፈጽሙ
የግል ጥቅማቸውን አካብተዋል የተባሉ ሌሎች ሁለት የሕንጻው የንግድ ቤቶች
ተከራዮችም በተመሳሳይ ቀን መያዛቸው ተመልክቷል፡፡
በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋሉበት ቀን ጀምሮ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ
የሚገኙት ዋና ጸሐፊው ዲያቆን ምሩፅ እና ሁለቱ ተጠርጣሪዎች፣ ሐምሌ ፲፮ ቀን
፳፻፭ ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ቦሌ
ምድብ ችሎት መቅረባቸው ተገልጧል፡፡
ዋና ጸሐፊውና የጥቅም ተባባሪዎቻቸው ፈጽመውታል የተባለውን ማጭበርበርና
ምዝበራ የሚያረጋግጡ የሰነድ ማስረጃዎችና የሰው ምስክሮች እንዳሉት ለችሎቱ የገለጸው ፖሊስ፣ በዋና ጸሐፊው ላይ
ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለማሰባሰብና የሰው ምስክሮችን ለማዘጋጀት የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችባቸው ክሥ እንደሌለና ከሣሻቸው እንደማይታወቅ በመጥቀስ የፖሊስን የተጨማሪ ጊዜ ጥያቄ
በጠበቃቸው በኩል የተቃወሙት ዲያቆን ምሩፅ÷ የሰባት ቤተሰብ አስተዳዳሪ መኾናቸውን፣ የሚጠየቁትን ማስረጃ
ቤተሰቦቻቸው እያቀረቡ መኾኑን፣ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ ቢሯቸውን ለመዝጋት እንዳልተፈቀደላቸው እና
ሐምሌ ፳፪ ቀን በደብሩ የቅዱስ ዑራኤል ክብረ በዓል በመኾኑ ሥራዎች እንዳይስተጓጎሉ በመጥቀስ የዋስትና
መብታቸው ተጠብቆ ጉዳያቸውን በውጭ መከታተል እንዲችሉ እንዲፈቀድላቸው አመልክተዋል፡፡ ዮሐንስ አይዳኝ
እና ዓለም ፍሥሓ የተባሉት ሁለቱ ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው፣ እነርሱ ውል የያዙበት ሰነድ ከሌሎች ተከራዮች
የተለየ እንዳልኾነ በመጥቀስ የዋስ መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል፡፡
የደብሩን ሕንጻ አራት የንግድ ሱቆች በተጭበረበረ ሰነድ በተፈጸመ የኪራይ ውል በመያዝ ሕገ ወጥ ጥቅም ሲያካብቱ
ቆይተዋል ከተባሉት ሁለት ተጠርጣሪዎች ተፈላጊውን ማስረጃ መሰብሰቡን የገለጸው ፖሊስ÷ ተጠርጣሪዎቹ
ለምርመራ ሥራው ጠቃሚ ማስረጃዎችን በመስጠት አደርገውታል ባለው መተባበር በዋስ ተለቀው በውጭ ኾነው
ጉዳያቸውን መከታተላቸውን እንደማይቃወም፣ ዋና ጸሐፊው ዲያቆን ምሩፅ ግን የደብሩ ጽ/ቤት ሓላፊ በመኾናቸው
በተለይ ከሒሳብ ምርመራ እንዳሸሿቸው የሚገመቱት የሙዳይ ምጽዋት ገንዘብ ቆጠራ ቃለ ጉባኤዎችእስኪገኙ ድረስ
‹‹ማስረጃ ያጠፋሉ፤ ምስክር ያባብላሉ›› በሚል የዋስትና ጥያቄያቸውን ተቃውሟል፡፡
ዮሐንስ አይዳኝና ዓለም ፍሥሓ የተባሉት ተከራዮች በብር 50 ሺሕ ዋስ እንዲለቀቁ ያዘዘው ፍ/ቤቱ፣ የዲያቆን ምሩፅን
የዋስትና ማመልከቻ ውድቅ በማድረግና የፖሊስን የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጥያቄ በመቀበል ተጠርጣሪው
ለሐምሌ ፴ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም እንዲቀርቡ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡
በቀደመው ዘገባችን እንዳስታውቅነው÷ ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት እና ከመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/
ቤት የተውጣጡ ልኡካንበደብሩ የፋይናንስ እንቅስቃሴና አሠራር ላይ ምርመራ እያካሄዱ ባሉበት ኹኔታ የደብሩ
ዋና ጸሐፊ ዲያቆን ምሩ
 
source... http://ethionetsa.blogspot.com/2013/07/blog-post_9460.html?spref=fb

No comments:

Post a Comment