Thursday, July 11, 2013

መምህርት ቤቲ

መምህርት ቤቲ ከደቡብ አፍሪቃ ውድድሯን አጠናቃ አዲስ አበባ አየር ማረፍያ ስትደርስ የኢፌድሪ ም/ጠ/ምኒስቴር የተከበሩ አቶ ደመቀ መኮንንን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት የተገኙበት ልዑካን ቡድን የአቀባበል ስነስርአት እንደሚያደርጉላት ቀልባችን ነገረን፡፡
• 8 ሰዎች ያሉት የተቀባይ ኮሚቴ እንዳቋቋሙ የነገሩን የባህልና ቱሪዝም ሚንስተር አቶ ባህሉ ይጠበቅ፤ ኮሚቴው ከተለያዩ የመጀመርያ ደረጃ ት/ቤቶች የተወጣጡ ከፍተኛ ውጤት ያገኙ ተማሪዎች ቤቲ ገና የአዲስ አበባን መሬት ስትረግጥ “ጀግና አይባረርም!” “ጀግና አይባረርም!” በሚል ሞቅ ያለ መፈክር እንደሚቀበሏት አስታውቀዋል፡፡ ኩታራዎቹ “ጀግና አይባረርም!” እያሉ ሲፎክሩ አጭር ምንሽር ይዞ በቀጭን ድምፅ “ከቢግ ብራዘር!!” እያለ የሚያጅብ ሰው ለማግኘትም ማስታወቅያ አውጥተው አመልካቾችን እየተጠባበቁ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
• የውሀና ኢነርጂ ምኒስተር በበኩላቸው ቤቲ በባኞ ቤት ውስጥ ከቦልት ጋር ስትላፋ የተቀረፀችበት ቪድዮ “Ethiopia is the water tower of Africa!” የሚለውን አባባል ከማረጋገጥ ባለፈ ስለ አካባቢ ጥበቃ ብዙ ልንማርበት እንደምንችል ገልፀውልናል፡፡
• የውጭ ጉዳይ ምኒስቴሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሀኖም ስነስርዐቱ ላይ የሚገኙት አቀባበል ለማድረግ ብቻ ሳይሆን የልጅቷን ጭንቅላት ጤንነት ለማረጋገጥም እንደሆነ ጭምጭምታዎች ሰምተናል፡፡
• በሌላ በኩል የሴራልዮኑ አምባሳደር ሚስተር ቡጁምቡራ ጆራራ የጥንዶቹ ግንኙነት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ወንድማዊ ግንኙነት ለማጠናከር የአንበሳውን ድርሻ እንደሚጫወት ገልፀው በቤቲ ማህፀን ውስጥ ለሚገኘው ፅንስም መንግስታቸው 300.000 የሴራልዮን ብር ለመስጠት መወሰኑን ተናግረዋል፡፡ ይህም ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር 18 ብር ከ35 ሳንቲም ሊደርስ እንደሚችል ሪፖርተራችን ከብሄራዊ ባንክ አረጋግጧል፡፡
• በተያያዘ ዜና ባልደረባችን አሸናፊ ጌታቸው ከመከላከያ ምኒስቴር ባደረሰን መረጃ ቤቲ ወደ አገርቤት ስትገባ 4 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ አስታውቋል፡፡ የተኩሱን አቅጣጫ ለማወቅ እና መከላከያው አይሮፕላኑን መቶ የመጣል ሀሳብ እንዳለው ለማጣራት ለጀነራል ሳሞራ የኑስ ደውለን ስልኩን አይመልሱም፡፡
• ሼክ መሀመድ አላሙዲ በበኩላቸው ለቤቲ የሚያስተላልፉት መልእክት ካላቸው ተጠይቀው ለቤቲ ሳይሆን ለሌሎች ባለስልጣናት እና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ “ባትጋሩኝ!” እንዳልኩ አስታውሱልኝ ብለውናል፡፡

No comments:

Post a Comment