Tuesday, July 30, 2013

ንዋዬ ቅድሳት ለማስጠበቅ የሚጥር ማኅበር፣


ንዋዬ ቅድሳት ለማስጠበቅ የሚጥር ማኅበር፣

የኢትዮጵያን አብያተ ክርስቲያን ንዋዬ ቅድሳትና የተለያዩ ቅርሶችን በሥርዓት ለመጠበቅ ባለመቻሉ፣ የሚያስጠብቅም ባለመኖሩ ፣ ባለፉት አያሌ ዓመታት እጅግ በዛ ያሉ ንዋዬ ቅድሳትና የተለያዩ የቤተክርስቲያኒቱ ቅርሶች ወደ ውጭ እየተጋዙ ገበያ ላይ መዋላቸው እንግዳ ነገር አልሆነም።
ከዚህ ቀደም ለቅርስ ጥበቃ ቆመናል የሚሉ ድርጅቶች ባይታጡም፣ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርሶች እንክብካቤና ልማት ማኅበር የተሰኘ አንድ ሌላ አዲስ ድርጅት መመሥረቱን ጌታቸው ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ የላከልን ዘገባ ያስረዳል። አዲሱ ማኅበር፤ አዲስ አበባ ውስጥ በኢንተር- ኮንቲኔንታል ሆቴል ባዘጋጀው የምክክር መድረክ፤ በህገ ወጥ መንገድ ቅርሶች ከሀገር የሚወጡበት ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ለይ መድረሱን ጥናት ያካሄዱ ምሁራን ገልጸዋል።
ጌታቸው ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ
አርያም ተክሌ
dw.de

No comments:

Post a Comment