Saturday, July 27, 2013

ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊው ፈላሻ ጠበቃውንና የጠበቃውን ሴት ልጅ ገደለ

ኢትዮጵያዊ-እስራኤላዊው ፈላሻ ጠበቃውንና የጠበቃውን ሴት ልጅ ገደለ


ማከሰኞ ጠዋት በፍች ጉዳይ ምክንያት በጠበቃው ክርክር የልረካው ኢትዮጵያዊ -እስራኤላዊ ጠበቃውንና የጠበቃውን ሴት ልጅ ገደለ፡፡
እስራኤላዊው የፖሊስ ቃል አቀባይ እንደተናገረው ተጠርጣሪው በአካባቢው በሚገኝ ህንፃ የጥበቃ ስራ ይሰራ እነደነበርና ከጠዋቱ 4፡00 ሰአት አካባቢ ግድያውን እንደፈጸመ ተናግሯል፡፡
ጌታጎን ታደሰ የተባለው ኢትዮጵያዊ -እስራኤላዊ የጥበቃ ሰራተኛ በፍች ሂደት ውስጥ እንደነበርና ሟች ጠበቃን ቀጠሮ ይከራከር እንደነበር የፖሊች ዘገባ ያስረዳል፡፡ ሆኖም ግን በፍርድ ሂደቱ ያልረካ በመሆኑ ጠበቃው ጋር ሄዶ የከፈለውን ብር እንዲመልስለት ጠይቆት እንደነበርና ቀጥሎም በያዘው መሳሪያ ጠበቃውንና ሴት ልጁን ከቅርብ ርቀት ተኩሶ እንደገደላቸው ተገልጿል፡፡
ኢትዮጵያዊ -እስራኤላዊም ወንጀሉን እንደፈጸመ በፖሊስ እንደተያዘና እርስ በረሱ የተቃረነ ማስረጃ እንደሰጠ የተዘገበ ሲሆን በወንጀሉ ወቅት አእምሮው ነትክክል እንደማያስብ ተናግሯል፡፡
ኢትዮጵያዊ -እስራኤላዊው ምንም አይነት የአእምሮ ህመም እንደሌለበትና የጥበቃ ስራውን ሲጀምር የተሰጠውን የአእምር,ሮ ጤንነት ፈተና አልፎ መሳሪያ እንደተሰጠው ተጠቅሷል፡፡ ይህንን ተከትሎ ዳኛው ሮብለት የአእምሮ ህመም ምርመራ እንዲያደርግና ለስምንት ተጨማሪ ቀናት እንዲቆይ ትዛዝ ሰጥተዋል፡፡
የ49 ዓመቱ ጌታጎን ታደሰ የ4 ልጆች አባትና በ2004 ዓ. ም. ከኢትየጵያ ወደ እስራኤል የመጣ ፈላሻ እንደሆነ መረጃዎቹ የጠቁማሉ፡፡
ማከሰኞና ባለፈው ግንቦት ወር ላይ በተፈጸመው ክስተት ምክንያት የእስራኤል ቁጥጥር ቢሮ በመሳሪያ አያያዝ ላይ የተሻሻለ ህግ እንደሚያስፈልግ ረቡእ እለት አስታውቋል፡፡ የሟች ጠበቃና የሴት ልጁ የቀብር ስነ-ስርዓትም በተመሳሳይ ቀን ሮብለት ተፈጽሟል፡፡

No comments:

Post a Comment