Thursday, July 25, 2013

እስላም ኦሮሞች፣ እስላም ያልሆኑ ኦሮሞች፣ ኦሮሞ ያልሆኑ እስላሞች እና ኢትዮጵያኖች ፣

እስላም ኦሮሞች፣ እስላም ያልሆኑ ኦሮሞች፣ ኦሮሞ ያልሆኑ እስላሞች እና ኢትዮጵያኖች ፣

(አዩም አያኔ ዘ ኢትዮጵያ)
ከላይ ያለዉ ቃል የተጳፈዉ በእንግሊዝኛ ነዉ። እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ። ዘሬም ነገዴም ከኢትዮጵያ ነዉ።ደግሞም ኦሮሞ ነኝ።
ለዝህ ጦማር መንሻ የሆነኝ አስከዛሬ ድረስ ኦሮሞ የሚባል አገር ፣ ወይንም ኦሮሞ የሚባል ዜግነት መኖሩን አለማዎቄ ነዉ። ኦሮሞ ነኝ በማለት ለነፃነት ቆረጠናል የሚሉትም የያዙት የኢትዮጵያን ፓስፖርት ነዉ።
እንግድህ ከላይ የትጳፈዉን ቃል የተጠቀመዉተ ጁሀር መሐመድ የተባለ ሰዉ ነዉ። ኦሮሞ ማለት አትዮጵያዊ አልምሆኑን ስለነግረኝ ፣ እኔ ደግሞ አትዮጵያዊ ሰልሆንኩ ፣ ኦሮሞ ሆኘ አና እሰላም ሳልሆን ግን አትዮጵያዊ መሆኔ እንደሱ አመለካከት ምን አንደሚባል ለማወቅ ነዉ። ወይንም ለመጠየቅ ነዉ።
ጁሀር መሐመድ፣
እኔ ኦሮሞ ነኝ፣ ያደኩት በኦሮሞቹ ዘሞዶቼ ተከብቤ ነዉ፣ የተወለደኩት የኦሮሞ ያልሆነ መሬት ላይ ነዉ። ኦሮሞ፣ አማራ፣ ሲዳማ፣ ከንባታ፣ ጉራጌ፣ ሀዲያ ፣ ዎላይታ፣ ሱማሌ፣ አደሬ ፣ አፋር፣ አና ሌሎችም ብዙ ጎሳዎች የሚኖሩባት አገር አለች ፣ እነዝህ ሁሉ አንድ ላይ ኢትዮጵያዊያኖች ተበልዉ የጠራሉ። ዜግነታቸዉም አትዮጵያዊ ነዉ። ላንተ ያለኝ ጥያቄ ሶስት ነዉ።
1. ለእስላም ኦሮሞች አና እስላም ላልሆኑ ኦሮሞች ያለህን ህልም ፣
2. እነዚሁ ሰዎች የትምድር ላይ አንድሚኖሩ አና
3. እስላም የሆኑም ያልሆኑ ኦሮሞዎች አትዮጵያዊ አንዳልሆኑ የገልጠልህን ነብይ ልትነግረኝ ትችል አንድሁ ብዬ ነዉ።
አትነገረግኝም ። ኦሮሞ ሰላልሆንክ የኦሮሞን ታሪክ አትዉቅም ። እስላምም ሰላልሆንክ ነብይህንም አታውቅም። ከሁሉም በላይ አትዮጵያዊነትን ስልምትጠላ ሰለኢትዮጵያ ነገድ ማዉራት አትቺልምና ነዉ። አኔ ግን እነግርሃለሁ። እስላም የሆኑም ያልሆኑም ኦርሞች ኢትዮጵያውያኖች አንድሆ ሰልማዉቅ ። ነብይህንም መገመት አይቅተኚም ቶራቦራ ሳልሄድ። ለዛረዉ ህልምህን ልንገርህና ሌላዉን ሌላ ቀን።
ሕልምህ እንድህ ነዉ፣
ከሰንሰልታማዉ የቶራቦራ ተራሮች የተነሳች ቁራ ወደላይ ትበርና የፓኪስታንን ምድር አቃርጣ ፣ የሳዑድን፣ የግብፅን ፣ የየመንን፣ የሶሪያን፣የኢራንን በረሃ አልፋ ቁልቁል አይትምዘገዘግች አንተ ነጭበነጭ ሺርጥ አሸርጠህ ኢቆምከበት ሠፈር በጥቁር ጨርቅ የተሸፈነ ስል ሜንጫ ታቀብልሃልች። ከዚያም ወደ ምእራብ አቅጣጫ አንድትመልከት ትነግረሃለች። አናም ታያልህ፣ ድምፅ ይመጣል ‘ሰ ‘ሰ ‘ ስራልዮን የሚል። ከዝያም “the bloody dimond” ፊልም ባይነህልናህ ይመጣል። ህልምህ የቀጥላል ፣ ሴት ሳይባል ወንድ፣ ህፃን ሳይባል ሺማገሌ በ AK 47 ኢንደቅጠል ሲረግፉ መካከል ሆንህ ሰትደሰት ደም አንደጎርፍ ስፈስ ፣ ለመሞት የምያጣጥሩትን ሰዎቺን አያስጎተትክ አጅ አጃቸዉን በሜንጫ ስትቀነጥስ።
ህልምህ የቀጥላል፣ ህፃናት ሴቶችና ወንዶች ሺማገሎዎችና አሮጊቶች ከንጎጆያቸዉ እንድቺቦ ስነዱ፣ በረት ከነከብቱ ፣ ጎተራ ክንእህሉ ስጋይ፣ መንደሩ በእቶን አሳት ስንበልበል ፣ ደስታህ ከፍ እያለ ህልምህ ይቀጥላል ። ህዝቡ ተሰብሰቦ ነብይ ሲያደርግህ፣ ወንዶቺን በሜንጫ አና በ AK-47 ስታስታጥቅ ፣ ሴቶቺን ከነነብሳቸዉ አስቀብረህ በድጋይ ሰታስዎግር ምኞትህ ስሰመር ፣ የቀጥላል ህልምህ ። ክርስትያን አምቦቃቅላ ሴቶች ስመጡልህ የስጋ ፍላጎትህን ጨርሰህ አንገታቸዎን ሰታስቀላ፣ ስትቀላ ።
ህልምህ የቀጥላል ፣ ቁራዉ ከንድምፁ ይመጣል ወደ ሰሜንም ዙር የልሃል ትዞራልህ፣ ቦ ቦ ቦ ቦኩሃራም ይልሃል የታይሃል። ታልማልህ ቤትክርስትያን በቦምብ ሰጋይ ፣ መስጊድ በፈንጂ ሰናድ ፣ አዉቶቡሶች ከነተሳፍርያቸዉ በሳት ስንበልበሉ ፣ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች ላይ ሰደርመሱ። የአበሻ ምደር ሰናጥ ፣ ደስታህ እየጨመረ ህልምህ የቀጥላል ። ቁራውም የመለሳል የጃራ አባገዳን ድምፅ ይዞ። የኔ ወራሽ ነህና የነገርኩህን ቀጥል አያለ ፣ የበደኖን የወተርን ፣ የአርባጉጉን ታርክ አትረሳ አያለ።ህልምህ የቀጥላል ፣ቁራዉ የመለሳል፣ በመለስም የመሰላል፣ የነወራሽነህና ኢትዮጵያን ያሉትን አሳድ ፣ አንገታቸዎን ቁረጥ ኢትዮጵያን አትራምስ፣ የደም መሬት የደም ምድርም አደርግ አያለ ።
ህልምህ የቀጥላል ፣ ቁራዉም የመጣል አሳፍሮህም ይከንፋል፣ ወደቶራቦራም ይበራል ። አዛም ጥቂት ታርፋለህ ህልምህንም ታጠናለህ አጥንተህም ታልማለህ ። በፓኪስታን በሳዑድ፣ በግብፅ ፣ ከፍ ከፍ ያለ ስፈራ ስሰጥህ ፣ ገንዘብም በገፍ ስጎርፍልህ፣ ህልምህ የቀጥላል። ቁራዉም ይመጣል ወደ ምስራቂም ዙር የልሃል። ትዞራለህ ኢትዮጵያንም ፣ታያለህ ። ባለጎፈረ ፈርሰኞች ሰጋልቡ ፣ ራባዶርንም ባራቴርንም ስያንበረክኩ፣ አረንጎዋዴ፣ ብጫ፣ ቀይ ቀለማትን የተሸለሙ የኦሮሞ ፈርሰኞች፣ ለመጀመርያ ጊዜ ነጭን ያንበርከኩ ፣ የጥቁር አንበሶች፣ ወዳንተ ስግሰግሱ ታያለህ አይተህም ትደነግጣለህ ደንግጠህም ትባንናለህ። ትናደዳለህ የበታችነትም ይሰማሀል ፣ተመልሰህም ትተኛለህ ። አንድገናም ታልማልህ፣ ኦሮሞ አማራ፣ጉራጌ፣ ከንባታ፣ ሀዲያ፣ ወላይታ፣ አደሬ ፣ ሱማሌ፣ ጋምቤላ ፣ሺናሻ፣ሲዳማ፣ትገሬ፣አፋር፣ ሌሎቺም ሌሎቺም አንድላይ ሆነዉ አንድላይቆመዉ አንድላይ ወድቀዉ ኢትዮጵያን ሲሉ ታያለህ አሁንም ተናደዳለህ ። ህልሙን ለማስተካከል ተመልሰህ ትተኛለህ ፣ አሁን ላትመለስ እንደ መለስ አንተም አስከ ወድያኛዉ ታሸልባልህ ፣ ኢትዮጵያ ግን ለዘላለም ትኖራለች፣ ከነልጆቹዋ ከእስላሞቹ ከክርስትያኞቹ ጋር። ያንተም የነብዮችህም ፣ የጃራም፣ የመለስም፣ የህወሃትም ፣የኦሆድድም፣የብአዴንም ህልማችሁ ህልም አንድሆነ ኢትዮጵያ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ ትኖራለች ተሻገራለች።
ከዝህ በላይ ባንተ ህልም ላይ ግዜ ማጥፋት እንዳንት ሃርቫርድ አንድመሄድ ከንቱ ስለሚሆን ብበቃኝስ ።

No comments:

Post a Comment